Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE

26/12/2024

Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction

02/12/2024

EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year

23/10/2024

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding

23/10/2024

A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs

14/10/2024

Congratulations !!

11/10/2024

EIIDE awarded its management and employees for the successful performance of the 2023/24 fiscal year

26/08/2024

EIIDE became the highest awardee of the Abyssinian Industrial Award

22/07/2024

Managers and employees of the Public Enterprises Holding and Administration and responsible institutions conducted sapling planting

20/07/2024

EIIDE conducted Ten-month plan implementation and 2024/25 corporate plan review of central and western districts

20/05/2024

EIIDE Reviewed it's Strategic Plan and other operating manuals

13/05/2024

EIIDE is Reviewing it's Strategic Plan and other operating manuals

10/05/2024

EIIDE participated in 'Ethiopia Tamrt' Expo

09/05/2024

EIIDE participated in the 10th International Cooperatives Exhibition and Bazaar

15/02/2024

Members of the Standing Committee on Trade and Industry of the House of peoples Representatives visited EIIDE

29/01/2024

EIIDE conducted Six month Plan performance Evaluation

17/01/2024

Sales Announcement

27/11/2023

Announcement regarding the supply of premix needed to enrich cooking oil with vitamins

06/11/2023

EIIDE evaluates its first quarter plan performance at Elilly Hotel

06/11/2023

EIIDE donated 4.2 million birr sanitary pad

17/10/2023

— 20 Items per Page
Showing 21 - 40 of 67 results.

ድርጅቱ ተልዕኮውን በተሟላ ሁኔታ ለማሳካትና በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪነቱን ለማጠናከር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ።

ይህ የተገለፀው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ) የ2018 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በገመገመበት ወቅት ነው።

‎የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ መለሰ መና እንደገለጹት፣ የተቋሙ የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግልጽ፣ ተዓማኒ እና የአመራር ቅንጅት የታየበት ነው።ተቋሙ ቀደም ሲል በከባድ ችግር ውስጥ እንደነበር ጠቅሰው፣ የአመራር ለውጥ በማድረግ ከዚያ ሁኔታ መውጣቱንና አሁን በተሻለ ሁኔታ እየሠራ መሆኑን ገልፀዋል።ተቋሙ የኦዲት ግኝቶችን በየጊዜው ማረም፣ በዓለም የሚኖረውን ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በመቋቋም ሽያጭና ትርፍን ማስቀጠል፣ አዳዲስ ደንበኞችን ማምጣት እና የገበያ ተደራሽነትን በሚዲያ መሣሪያዎች ማሳደግ እንደ ጠንካራ አፈፃፀሞች ተጠቁመዋል።

‎እንዲሁም በግዥና ሽያጭ ሂደቶች ጥራትን ማረጋገጥ፣ የሴቶች የአመራር ተሳትፎን ማሳደግ እና የሰው ሀብት ልማት ሥርዓቱን ማጠናከር ተቋሙን ለሌሎች ድርጅቶች አርአያ የሚያደርገው መሆኑን ገልፀዋል። በተጨማሪም የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ለመተግበር የተደረጉ ዝግጅቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል።

‎‎ድርጅቱን በቀጣይ የሀብት አስተዳደርን ማሻሻል፣ የቅርንጫፍ ቢሮዎችን ማዘመን እና የዲጂታል ስርዓት ለማስፋት የተጀመሩ ሥራዎች እንዲጠናከሩ አሳስበዋል።‎የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ኢንጅነር ስለሺ ኮሬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ተቋሙ ከቋሚ ኮሚቴው ጋር ይበልጥ በመተባበር ለለውጥ የሚሠራ መሆኑን ገልፀው፣ ችግሮችን በጥናት፣ በዘላቂነትና በአስተማማኝ መልኩ ከሥር መሠረቱ ለመፍታት በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ያስጠናቸው ጥናቶች ጥሩ መሆናቸውን ገልፀዋል። ይህንን ጥናት በማስተባበርና በማረጋገጥ ወደ ሥራ መግባት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

‎በግዥ፣ በሽያጭና በተደራሽነት ዘርፎች የተቋሙ እቅዶችና አፈጻጸሞች የተሻሻሉ መሆናቸውን፣ ከኦዲት ጋር ተያይዞ የነበሩ ችግሮችም በተገቢ መንገድ መፍታታቸውን ገልፀው፤ ተቋሙን ለመለወጥ እና ሀብት ለማፍራት የሚደረጉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ይህንኑ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።‎ገበያውንና ወቅቱን በማየት የድርጅቱን ሕንጻ ዲዛይን በመቀየር ሙሉ በሙሉ ወደ ቢሮ አገልግሎት ለመለወጥ የተደረጉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን እና ቀሪ የግንባታ ሥራዎችን በፍጥነት ማጠናቀቅ እንደሚገባም አስረድተዋል።

በቀጣይ የድርጅቱን ይዞታ ማስከበር፣ የኢንዱስትሪ ጨው ግብዓት አቅርቦት አማራጮችን ማስፋት ትኩረት ሊደረግባቸው ይገባል ብለዋል።‎የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ዳዊት አዳነ በበኩላቸው፤ ድርጅቱ ብቃት ባለው የሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት፣ ጠንካራ የአቅርቦትና የግብይት ሰንሰለት በመገንባት፣ ጥራታቸውን የጠበቁ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን በማልማትና በማቅረብ እንዲሁም የተመረጡ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማድረስ፣ የሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ውጤታማነት እንዲጨምር እና የገበያ መረጋጋት እንዲፈጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

‎‎ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት 9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙ በኢንዱስትሪ ግብዓቶች እና ውጤቶች ግዥ እና ሽያጭ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡን ጠቁመው፣ ተቋሙ በበጀት አመቱ 580 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ለቋሚ ኮሚቴው ተናግረዋል።‎በበጀት ዓመቱ ለኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆን ምክንያት የነበሩ ጉዳዮችን በቀጣይ በመፍታት የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ጥረት የሚደረግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡