የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ

EIIDE offered 16.5 million liters of edible oil at a reasonable price
14/09/2023

EIIDE conducted an evaluation of the of the 2022/23 fiscal year plan and the next year's plan of the enterprise
23/08/2023

Members of the Management Board visited projects of EIIDE
31/07/2023

Managers and Employees of EIIDE Conducted Green Legacy
27/07/2023

EIIDE has launched a women's workers forum
20/07/2023

ኢኢግልድ የ2015 በጀት ዓመት የስምንት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
11/04/2023

ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ
23/03/2023

ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ
18/01/2023

አርአያነት ያለው ተግባር
14/09/2022

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፍጆታ ምርቶች መሸጫ ዋጋ
09/09/2022

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ
29/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ
07/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ9ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ ምርትና አገልግሎቱን አስተዋወቀ
09/02/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ብር 265 ሚሊዮን የተጣራ ትርፍ ማግኘቱ ተገለጸ
07/02/2022

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት የሚያቀርቡ አካላት ከህገወጥ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ጥሪ ቀረበ
30/12/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ
12/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት 2 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ድጋፍ ለሃገር መከላከያ ሠራዊት ሰጠ::
02/09/2021

የኢኢግልድ አመራሮች በወረኢሉ ግንባር በመገኘት ለመከላከያ ሠራዊት ድጋፍ አበረከቱ::
02/09/2021

ኢኢግልድ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ
02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ነጩ ፖስታ ለነጩ ቤተመንግስት መርሃ ግብርን አካሄዱ
02/09/2021
ኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የዲስትሪክት ሃላፊዎችና ፈጻሚዎች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድን በላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የሚጠበቅባቸውን ሃለፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ፡፡
ይህ የተገለጸው የድርጅቱ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም፣ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድና በጸደቁ የድርጅቱ አራት የሥራ መመሪያዎች ላይ የማዕከላዊ፣ የምዕራብ፣ የምስራቅና ፣የሰሜንና የደቡብ ዲስትሪክቶች ሃላፊዎችና አመራሮች በተሳተፉበት ከነሐሴ 21-22 እንዲሁም ከነሐሴ 28-29ቀን 2014 ዓ.ም በሐዋሳ፣ ጅማ እና ቢሾፍቱ እና ባህር ዳር ከተሞች ባካሄዱት የምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡
በተካሄዱት የውይይት መድረኮች የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በተለይ በሐዋሳ መድረክ ላይ እንደገለጹት በውይይት መድረኩ አመራሮች እና ፈጻሚዎች በአፈጻጸም ሂደት የነበሯቸውን ሚና፣ ጥንካሬዎቻቸውንና ክፍተቶቻቸውን የገመገሙበትና ጠንካራ ጎኖቻቸውን አጠናክረው ለመቀጠል የጋራ መግባባት የተደረሰበት መድረክ እንደሆነ እንዲሁም የታዩ ክፍተቶች ታርመው በ2015 በጀት ዓመት ታላላቅ ዕቅዶችን ለማሳካት ሁሉም የድርሻውን በጋራ እና በተቀናጀ መልኩ የድርጅቱን ተልዕኮ ለማሳካት የጋራ ስምምነት የተደረሰበት መድረክ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡
በተያያዘም የድርጅቱ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ግዢና ሽያጭ ዘርፍ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ግርሻ በጅማ ከተማ በተካሄደው መድረክ የበላይ አመራሮች የዲስትሪክት ሃላፊዎችና ፈጻሚዎች በግንባር ተገናኝተው በ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2015 ዕቅድ እንዲሁም በተሻሻሉ መመሪያዎች ላይ መወያየታቸው እንደ ትልቅ የንግድ ድርጅት እየተካሄዱ ያሉትን የሪፎርም ሥራዎች በአግባቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ በተጨማሪም የ2015 በጀት ዓመት ዕቅዶችን በውጤታማነት ለመተግበር የዚህ ዓይነት መድረኮች የራሱ ሚና ያለው እንዳለው ያብራሩት አቶ ሰለሞን ቀደም ሲል ከነበረው ልማዳዊ አሠራርና አካሄድ ተወጥቶ እንደድርጅት የምንታደስበትን ጎዳና የምንይዝበት መድረክ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
በምክክር መድረኮቹ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በዝርዝር ቀርቦ ውይይት የተካሄዶበታል፡፡ በተጨማሪም በአፈጻጸም ሂደት እንቅፋት የነበሩ የስራ መመሪያዎች ከወቅቱ የድርጅቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣሙ ተደርገው የጸደቁ የስራ መመሪያዎች፤ የዲስትሪክት ሃላፊዎችና የሽያጭ ባለሙያዎች በተሳተፉባቸው መድረኮች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በመድረኮቹ የግዢ፣ የሽያጭ የፋይናንስ እና የንብረት አወጋገድ መመሪያዎች ቀርበው ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎች ተከናውኗል፡፡
በማጠቃለያም በውይይት መድረኮቹ ተሳታፊ የነበሩ የድርጅቱ የበላይና መካከለኛ አመራሮች፣ የዲስትሪክት ሃላፊዎች፣ የቡድን መሪዎች እና ባለሙያዎች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድን በላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የሚጠበቅባቸውን ሃለፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡