Recognition was given to districts and branches that achieved outstanding performance in six months.

27/01/2026

Training on procurement performance guidelines and change management has been given

10/11/2025

EIIDE's first quarter performance was announced as successful.

20/10/2025

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) Receives Platinum Level Award

10/10/2025

Managers and experts of Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) participated on training held at the African Leadership Excellence Academy

25/09/2025

EIIDE Yarn Processing Center staffs conducted field visits

23/09/2025

EIIDE leaders and employees celebrated the completion of the Grand Renaissance Dam and annual workers' day

09/09/2025

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise (EIIDE) highlighted for strong performance for the 2024/25 budget year

27/08/2025

Financial and Audit Report 2021/22

12/05/2025

Nine-month Performance Review Session Highlights Considerable Achievements

21/04/2025

EIIDE leaders and employees celebrated International Women's Day.

17/03/2025

EIIDE conducted Eight-month plan performance review

17/03/2025

Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given

11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21

28/01/2025

Financial and Audit Report

25/10/2023

Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE

26/12/2024

Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction

02/12/2024

EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year

23/10/2024

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding

23/10/2024

A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs

14/10/2024

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 62 results.

ኢኢግልድ በየወሩ 52,080 ኩንታል የኢንዱስትሪ ጨው ለቆዳ ፋብሪካዎች ለማቅረብ የግዢ ውል ተፈራረመ

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ለቆዳ ኢንዱስትሪዎች በግብዓትነት የሚያገለግል 52,080 ኩንታል የኢንዱሰትሪ ጨው በግዢ በየወሩ ለማቅረብ በአፋር ክልል ከሚገኝ አፍዴራ የጨው አምራቾች የህብረት ስራ ማህበር ጋር የስምምነት ውል ሚያዚያ 11 ቀን 2013 ዓ.ም ተፈራረመ፡፡ 


የውል ስምምነቱ መሠረት ኢኢግልድ ከአፍዴራ ጨው አምራቾች የህብረት ስራ ማህበር በየወሩ 52,080 ኩንታል በመግዛት ስምምነት ላይ የደረሰና ለተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ እየሠራ ይገኛል፡፡
ለዚህም ተፈጻሚነት እንዲረዳ ትራንስፖርተሮችን በማመቻቸት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነና ለዘንድሮውም የትንሠኤ በዓልና የረመዳን በዓል በሚፈጸም እርድ ቆዳ እንደይባክንና እንዳይጣል አስቸኳይ ግዢ በመፈጸም ጨው ወደ ገበያው እንዲገባ ተደርጓል፡፡


ከውል ስምምነት መፈራረም በኋላ 1,680 ኩንታል ጨው ተጓጉዞ በድርጅታችን የቃሊቲ የሽያጭ ቅርንጫፍ መጋዘን ተራግፏል፡፡


በተጨማሪም በግዢ ሂደት ላይ የሚገኘው ጨው የድርጅታችን እና የጨው አምራቹ የህብረት ስራ ማህበር ስምና ሎጎ ጎን ለጎን በሚታተምበት ማሸጊያ የሚታሸግ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ለምግብነትም እንዳይውል በጨዉ ላይ ኬሚካል እንደተጨመርበትና ይህም በማሸጊያው ላይ መገለጹ ተብራርቷል፡፡ 
በተያያዘም ድርጅታችን በየወሩ 52,080 ኩንታል በመግዛት ለተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ትራንስፖርተሮችን በማመቻቸት የተሰራ ቢሆንም የኢንዱስትሪ ጨውን ለማቅረብ የተስማማው የአምራቾች ማህበር በታቀደው መጠን ድርጅታችን ባቀረባቸው የትራንስፖርት ተሸከርካሪዎችና የጨው ማሸጊያ ከረጢት መጠን በሚፈለገው ፍጥነት ያለማከናወን ክፍተቶች እንደሆነ ታውቋል፡፡ በተለይም አምራች ማህበራቱ በቂ የሰው ሃይል አሰማርቶ ስራውን ያለማከናወንና ምርቱን ለማቅረብ በቂ ዝግጅት አለማድረግ በዋናነት የታዩ ችግሮች እንደሆኑም ተገልጿል፡፡


በመሆኑም የታየውን የአሰራር ክፍተት በመረዳት የኢኢግልድ ከፍተኛና መካከለኛ አመራርሮች ከአፋር ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ አመራሮችና ጨውን ለማምረት ስምምነት ከገባው አፍዴራ የጨው አምራቾች ሃላ/የተ የግል ማህበር አመራሮች ጋር በታዩት ችግሮች ዙሪያ በመወያየት ለመፍታት በስፍራው ይገኛሉ፡፡ 
ኢኢግልድ ለአምራች ኢንዱስትሪዎቻችን ግብዓት በማቅረብ በዘርፉ የሚታየውን የኢንዱስትሪ ግብዓቶች እጥረት ክፍተት ለመሙላት የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡