ኢኢግልድ በየወሩ 52,080 ኩንታል የኢንዱስትሪ ጨው ለቆዳ ፋብሪካዎች ለማቅረብ የግዢ ውል ተፈራረመ

Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given
11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025

Financial and Audit Report
25/10/2023

Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE
26/12/2024

Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction
02/12/2024

EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year
23/10/2024

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding
23/10/2024

A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs
14/10/2024

Congratulations !!
11/10/2024

EIIDE awarded its management and employees for the successful performance of the 2023/24 fiscal year
26/08/2024

EIIDE became the highest awardee of the Abyssinian Industrial Award
22/07/2024

Managers and employees of the Public Enterprises Holding and Administration and responsible institutions conducted sapling planting
20/07/2024

EIIDE conducted Ten-month plan implementation and 2024/25 corporate plan review of central and western districts
20/05/2024

EIIDE Reviewed it's Strategic Plan and other operating manuals
13/05/2024

EIIDE is Reviewing it's Strategic Plan and other operating manuals
10/05/2024

EIIDE participated in 'Ethiopia Tamrt' Expo
09/05/2024

EIIDE participated in the 10th International Cooperatives Exhibition and Bazaar
15/02/2024

Members of the Standing Committee on Trade and Industry of the House of peoples Representatives visited EIIDE
29/01/2024

EIIDE conducted Six month Plan performance Evaluation
17/01/2024

Sales Announcement
27/11/2023
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ለቆዳ ኢንዱስትሪዎች በግብዓትነት የሚያገለግል 52,080 ኩንታል የኢንዱሰትሪ ጨው በግዢ በየወሩ ለማቅረብ በአፋር ክልል ከሚገኝ አፍዴራ የጨው አምራቾች የህብረት ስራ ማህበር ጋር የስምምነት ውል ሚያዚያ 11 ቀን 2013 ዓ.ም ተፈራረመ፡፡
የውል ስምምነቱ መሠረት ኢኢግልድ ከአፍዴራ ጨው አምራቾች የህብረት ስራ ማህበር በየወሩ 52,080 ኩንታል በመግዛት ስምምነት ላይ የደረሰና ለተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ እየሠራ ይገኛል፡፡
ለዚህም ተፈጻሚነት እንዲረዳ ትራንስፖርተሮችን በማመቻቸት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነና ለዘንድሮውም የትንሠኤ በዓልና የረመዳን በዓል በሚፈጸም እርድ ቆዳ እንደይባክንና እንዳይጣል አስቸኳይ ግዢ በመፈጸም ጨው ወደ ገበያው እንዲገባ ተደርጓል፡፡
ከውል ስምምነት መፈራረም በኋላ 1,680 ኩንታል ጨው ተጓጉዞ በድርጅታችን የቃሊቲ የሽያጭ ቅርንጫፍ መጋዘን ተራግፏል፡፡
በተጨማሪም በግዢ ሂደት ላይ የሚገኘው ጨው የድርጅታችን እና የጨው አምራቹ የህብረት ስራ ማህበር ስምና ሎጎ ጎን ለጎን በሚታተምበት ማሸጊያ የሚታሸግ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ለምግብነትም እንዳይውል በጨዉ ላይ ኬሚካል እንደተጨመርበትና ይህም በማሸጊያው ላይ መገለጹ ተብራርቷል፡፡
በተያያዘም ድርጅታችን በየወሩ 52,080 ኩንታል በመግዛት ለተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ትራንስፖርተሮችን በማመቻቸት የተሰራ ቢሆንም የኢንዱስትሪ ጨውን ለማቅረብ የተስማማው የአምራቾች ማህበር በታቀደው መጠን ድርጅታችን ባቀረባቸው የትራንስፖርት ተሸከርካሪዎችና የጨው ማሸጊያ ከረጢት መጠን በሚፈለገው ፍጥነት ያለማከናወን ክፍተቶች እንደሆነ ታውቋል፡፡ በተለይም አምራች ማህበራቱ በቂ የሰው ሃይል አሰማርቶ ስራውን ያለማከናወንና ምርቱን ለማቅረብ በቂ ዝግጅት አለማድረግ በዋናነት የታዩ ችግሮች እንደሆኑም ተገልጿል፡፡
በመሆኑም የታየውን የአሰራር ክፍተት በመረዳት የኢኢግልድ ከፍተኛና መካከለኛ አመራርሮች ከአፋር ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ አመራሮችና ጨውን ለማምረት ስምምነት ከገባው አፍዴራ የጨው አምራቾች ሃላ/የተ የግል ማህበር አመራሮች ጋር በታዩት ችግሮች ዙሪያ በመወያየት ለመፍታት በስፍራው ይገኛሉ፡፡
ኢኢግልድ ለአምራች ኢንዱስትሪዎቻችን ግብዓት በማቅረብ በዘርፉ የሚታየውን የኢንዱስትሪ ግብዓቶች እጥረት ክፍተት ለመሙላት የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡