ኢኢግልድ በየወሩ 52,080 ኩንታል የኢንዱስትሪ ጨው ለቆዳ ፋብሪካዎች ለማቅረብ የግዢ ውል ተፈራረመ
Recognition was given to districts and branches that achieved outstanding performance in six months.
27/01/2026
Training on procurement performance guidelines and change management has been given
10/11/2025
EIIDE's first quarter performance was announced as successful.
20/10/2025
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) Receives Platinum Level Award
10/10/2025
Managers and experts of Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) participated on training held at the African Leadership Excellence Academy
25/09/2025
EIIDE Yarn Processing Center staffs conducted field visits
23/09/2025
EIIDE leaders and employees celebrated the completion of the Grand Renaissance Dam and annual workers' day
09/09/2025
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise (EIIDE) highlighted for strong performance for the 2024/25 budget year
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
Nine-month Performance Review Session Highlights Considerable Achievements
21/04/2025
EIIDE leaders and employees celebrated International Women's Day.
17/03/2025
EIIDE conducted Eight-month plan performance review
17/03/2025
Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
Financial and Audit Report
25/10/2023
Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE
26/12/2024
Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction
02/12/2024
EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year
23/10/2024
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding
23/10/2024
A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs
14/10/2024
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ለቆዳ ኢንዱስትሪዎች በግብዓትነት የሚያገለግል 52,080 ኩንታል የኢንዱሰትሪ ጨው በግዢ በየወሩ ለማቅረብ በአፋር ክልል ከሚገኝ አፍዴራ የጨው አምራቾች የህብረት ስራ ማህበር ጋር የስምምነት ውል ሚያዚያ 11 ቀን 2013 ዓ.ም ተፈራረመ፡፡
የውል ስምምነቱ መሠረት ኢኢግልድ ከአፍዴራ ጨው አምራቾች የህብረት ስራ ማህበር በየወሩ 52,080 ኩንታል በመግዛት ስምምነት ላይ የደረሰና ለተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ እየሠራ ይገኛል፡፡
ለዚህም ተፈጻሚነት እንዲረዳ ትራንስፖርተሮችን በማመቻቸት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነና ለዘንድሮውም የትንሠኤ በዓልና የረመዳን በዓል በሚፈጸም እርድ ቆዳ እንደይባክንና እንዳይጣል አስቸኳይ ግዢ በመፈጸም ጨው ወደ ገበያው እንዲገባ ተደርጓል፡፡
ከውል ስምምነት መፈራረም በኋላ 1,680 ኩንታል ጨው ተጓጉዞ በድርጅታችን የቃሊቲ የሽያጭ ቅርንጫፍ መጋዘን ተራግፏል፡፡
በተጨማሪም በግዢ ሂደት ላይ የሚገኘው ጨው የድርጅታችን እና የጨው አምራቹ የህብረት ስራ ማህበር ስምና ሎጎ ጎን ለጎን በሚታተምበት ማሸጊያ የሚታሸግ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ለምግብነትም እንዳይውል በጨዉ ላይ ኬሚካል እንደተጨመርበትና ይህም በማሸጊያው ላይ መገለጹ ተብራርቷል፡፡
በተያያዘም ድርጅታችን በየወሩ 52,080 ኩንታል በመግዛት ለተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ትራንስፖርተሮችን በማመቻቸት የተሰራ ቢሆንም የኢንዱስትሪ ጨውን ለማቅረብ የተስማማው የአምራቾች ማህበር በታቀደው መጠን ድርጅታችን ባቀረባቸው የትራንስፖርት ተሸከርካሪዎችና የጨው ማሸጊያ ከረጢት መጠን በሚፈለገው ፍጥነት ያለማከናወን ክፍተቶች እንደሆነ ታውቋል፡፡ በተለይም አምራች ማህበራቱ በቂ የሰው ሃይል አሰማርቶ ስራውን ያለማከናወንና ምርቱን ለማቅረብ በቂ ዝግጅት አለማድረግ በዋናነት የታዩ ችግሮች እንደሆኑም ተገልጿል፡፡
በመሆኑም የታየውን የአሰራር ክፍተት በመረዳት የኢኢግልድ ከፍተኛና መካከለኛ አመራርሮች ከአፋር ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ አመራሮችና ጨውን ለማምረት ስምምነት ከገባው አፍዴራ የጨው አምራቾች ሃላ/የተ የግል ማህበር አመራሮች ጋር በታዩት ችግሮች ዙሪያ በመወያየት ለመፍታት በስፍራው ይገኛሉ፡፡
ኢኢግልድ ለአምራች ኢንዱስትሪዎቻችን ግብዓት በማቅረብ በዘርፉ የሚታየውን የኢንዱስትሪ ግብዓቶች እጥረት ክፍተት ለመሙላት የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡