ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ

18/01/2023

አርአያነት ያለው ተግባር

14/09/2022

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፍጆታ ምርቶች መሸጫ ዋጋ

09/09/2022

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ

29/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ

07/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ9ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ ምርትና አገልግሎቱን አስተዋወቀ

11/02/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ብር 265 ሚሊዮን የተጣራ ትርፍ ማግኘቱ ተገለጸ

04/02/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ

12/08/2022

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት የሚያቀርቡ አካላት ከህገወጥ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ጥሪ ቀረበ::

02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አምስት ወራት አፈጻጸሙን ገመገመ::

02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት 2 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ድጋፍ ለሃገር መከላከያ ሠራዊት ሰጠ::

02/09/2021

የኢኢግልድ አመራሮች በወረኢሉ ግንባር በመገኘት ለመከላከያ ሠራዊት ድጋፍ አበረከቱ::

02/09/2021

ኢኢግልድ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ

02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ነጩ ፖስታ ለነጩ ቤተመንግስት መርሃ ግብርን አካሄዱ

02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ የግንባታ የስምምነት ውል ተፈራረመ፡፡

02/09/2021

ከውጪ አገር ከተገዛው ዘይት 5.8 ሚሊየን ሊትር መግባቱ ተገለፀ።

02/09/2021

ኢኢግልድ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ሰጠ::

02/09/2021

ኢኢግልድ ለመንግስትና የግል ድርጅቶች ሠራተኞች የስንዴ ዱቄት በተመጣጣኝ ዋጋ አቀረበ

02/09/2021

ኢኢግልድ በየወሩ 52,080 ኩንታል የኢንዱስትሪ ጨው ለቆዳ ፋብሪካዎች ለማቅረብ የግዢ ውል ተፈራረመ

02/09/2021

ኢኢግልድ ከ2.7 ቢሊዮን ብር በላይ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችና ውጤቶችን አቀረበ

02/09/2021

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 21 results.

ኢኢግልድ በየወሩ 52,080 ኩንታል የኢንዱስትሪ ጨው ለቆዳ ፋብሪካዎች ለማቅረብ የግዢ ውል ተፈራረመ

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ለቆዳ ኢንዱስትሪዎች በግብዓትነት የሚያገለግል 52,080 ኩንታል የኢንዱሰትሪ ጨው በግዢ በየወሩ ለማቅረብ በአፋር ክልል ከሚገኝ አፍዴራ የጨው አምራቾች የህብረት ስራ ማህበር ጋር የስምምነት ውል ሚያዚያ 11 ቀን 2013 ዓ.ም ተፈራረመ፡፡ 


የውል ስምምነቱ መሠረት ኢኢግልድ ከአፍዴራ ጨው አምራቾች የህብረት ስራ ማህበር በየወሩ 52,080 ኩንታል በመግዛት ስምምነት ላይ የደረሰና ለተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ እየሠራ ይገኛል፡፡
ለዚህም ተፈጻሚነት እንዲረዳ ትራንስፖርተሮችን በማመቻቸት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነና ለዘንድሮውም የትንሠኤ በዓልና የረመዳን በዓል በሚፈጸም እርድ ቆዳ እንደይባክንና እንዳይጣል አስቸኳይ ግዢ በመፈጸም ጨው ወደ ገበያው እንዲገባ ተደርጓል፡፡


ከውል ስምምነት መፈራረም በኋላ 1,680 ኩንታል ጨው ተጓጉዞ በድርጅታችን የቃሊቲ የሽያጭ ቅርንጫፍ መጋዘን ተራግፏል፡፡


በተጨማሪም በግዢ ሂደት ላይ የሚገኘው ጨው የድርጅታችን እና የጨው አምራቹ የህብረት ስራ ማህበር ስምና ሎጎ ጎን ለጎን በሚታተምበት ማሸጊያ የሚታሸግ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ለምግብነትም እንዳይውል በጨዉ ላይ ኬሚካል እንደተጨመርበትና ይህም በማሸጊያው ላይ መገለጹ ተብራርቷል፡፡ 
በተያያዘም ድርጅታችን በየወሩ 52,080 ኩንታል በመግዛት ለተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ትራንስፖርተሮችን በማመቻቸት የተሰራ ቢሆንም የኢንዱስትሪ ጨውን ለማቅረብ የተስማማው የአምራቾች ማህበር በታቀደው መጠን ድርጅታችን ባቀረባቸው የትራንስፖርት ተሸከርካሪዎችና የጨው ማሸጊያ ከረጢት መጠን በሚፈለገው ፍጥነት ያለማከናወን ክፍተቶች እንደሆነ ታውቋል፡፡ በተለይም አምራች ማህበራቱ በቂ የሰው ሃይል አሰማርቶ ስራውን ያለማከናወንና ምርቱን ለማቅረብ በቂ ዝግጅት አለማድረግ በዋናነት የታዩ ችግሮች እንደሆኑም ተገልጿል፡፡


በመሆኑም የታየውን የአሰራር ክፍተት በመረዳት የኢኢግልድ ከፍተኛና መካከለኛ አመራርሮች ከአፋር ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ አመራሮችና ጨውን ለማምረት ስምምነት ከገባው አፍዴራ የጨው አምራቾች ሃላ/የተ የግል ማህበር አመራሮች ጋር በታዩት ችግሮች ዙሪያ በመወያየት ለመፍታት በስፍራው ይገኛሉ፡፡ 
ኢኢግልድ ለአምራች ኢንዱስትሪዎቻችን ግብዓት በማቅረብ በዘርፉ የሚታየውን የኢንዱስትሪ ግብዓቶች እጥረት ክፍተት ለመሙላት የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡