ኢኢግልድ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ሰጠ::

ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ
18/01/2023

አርአያነት ያለው ተግባር
14/09/2022

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፍጆታ ምርቶች መሸጫ ዋጋ
09/09/2022

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ
29/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ
07/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ9ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ ምርትና አገልግሎቱን አስተዋወቀ
11/02/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ብር 265 ሚሊዮን የተጣራ ትርፍ ማግኘቱ ተገለጸ
04/02/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ
12/08/2022

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት የሚያቀርቡ አካላት ከህገወጥ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ጥሪ ቀረበ::
02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አምስት ወራት አፈጻጸሙን ገመገመ::
02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት 2 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ድጋፍ ለሃገር መከላከያ ሠራዊት ሰጠ::
02/09/2021

የኢኢግልድ አመራሮች በወረኢሉ ግንባር በመገኘት ለመከላከያ ሠራዊት ድጋፍ አበረከቱ::
02/09/2021

ኢኢግልድ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ
02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ነጩ ፖስታ ለነጩ ቤተመንግስት መርሃ ግብርን አካሄዱ
02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ የግንባታ የስምምነት ውል ተፈራረመ፡፡
02/09/2021

ከውጪ አገር ከተገዛው ዘይት 5.8 ሚሊየን ሊትር መግባቱ ተገለፀ።
02/09/2021

ኢኢግልድ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ሰጠ::
02/09/2021

ኢኢግልድ ለመንግስትና የግል ድርጅቶች ሠራተኞች የስንዴ ዱቄት በተመጣጣኝ ዋጋ አቀረበ
02/09/2021

ኢኢግልድ በየወሩ 52,080 ኩንታል የኢንዱስትሪ ጨው ለቆዳ ፋብሪካዎች ለማቅረብ የግዢ ውል ተፈራረመ
02/09/2021

ኢኢግልድ ከ2.7 ቢሊዮን ብር በላይ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችና ውጤቶችን አቀረበ
02/09/2021
ኢኢግልድ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ሰጠ
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢኢግልድ) እየተካሄደ ያለውን የሀገር ህልውናን የማዳን ዘመቻ መነሻ በማድረግ ሀገር ለመከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ እና ድርጅቱ በ2013 በጀት ዓመት ያስመዘገበውን አጥጋቢ ውጤት ምክንያት በማድረግ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የድርጅቱ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ነሐሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም ሰጠ፡፡
ለሠራዊታችን ድጋፉ የተሰጠው ኢኢግልድ በ2013 በጀት ዓመት ያስመዘገበውን የላቀ አፈጻጸም ምክንያት በማድረግ በድርጅቱ ቅጥር ጊቢ አጥጋቢ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች ዕውቅናና ሽልማት ለመስጠት ባዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ ሲሆን በሥነሥርዓቱም ላይ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ክብርት ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ተወካይ አስረክበዋል፡፡
በድጋፍ አሰጣጡ ስነስርዓት ላይ ከሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የመከላከያ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ ብ/ጄነራል አስረስ አያሌው እእንደገለጹት ከሀገራችን የቅርብ፣ የሩቅ የውስጥ ጠላቶች ጋር በማበር ሀገር ለማፈራረስ እየሰራ የሚገኘው ፀረ-ህዝብ ቡድን ለማስወገድ ሠራዊቱ ቀን ከሌሊት እየተዋደቀ የሚገኝ ሲሆን በተለይ ይህ ህገ ወጥ ቡድን በአማራና አፋር በአጎራባች ስፍራዎች ጥቃቱን ለማስፋፋት የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ለመግታት በሰራዊቱ የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኖች ከሠጡት የቁሳቁስ ድጋፍ በተጨማሪ አሁን በገንዘብ ተደረገው የ2 ሚሊየን ብር ድጋፍና በድርጅቱ ከሚሰሩ ሠራተኞች መካከል በፈቃደኝነት ለመዝመት መነሳሳታቸው ለሰራዊቱ ተጨማሪ ስንቅ እንደሚሆነው ሃላፊው አመልክተዋል፡፡
በተያያዘም በዋናነት ድርጅቱ የ2013 በጀት ዓመት ያስመዘገበውን የላቀ ውጤት መነሻ በማድረግ ባካሄደው የእውቅናና የሽልማት መርሃግብር የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መላኩ አለበል፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታና የኢኢግልድ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ተካ ገ/የስ እንዲሁም የተከበሩ ወ/ሮ መሠረት አባተ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ኢንዱስትሪ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የኢኢግልድ የስራ አመራር ቦርድ አባላት ተገኝተዋል፡፡
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በዕውቅናና ሽልማት ስነስርት ላይ አገራችን በሪፎርም ውስጥ እንደምትገኝ አመልክተው በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ፣ በመከላከያ እና በሌሎችም ዘርፎች እተካሄደ ያለው ሪፎርም ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነና በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ውስጥ እየተካሄደ ያለው የሪፎርም ሥራ በተለይም በአመራር፣ በአሰራር፣ በቴክኖሎጂ እና በዲጂታል አውቶሜሽን ስራዎች የሚያበረታቱና ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ ላስመዘገበው ውጤት አስዋጽኦ እንዳላቸው አመልክተዋል፡፡
ኢኢግልድ ባለፉት ዓመታት የነበሩበትን የተወሳሰቡ ችግሮች በአብዛኛው እንደተወጣና በተካሄዱትም የለውጥ ስራዎች ድርጅቱን ከውድቀት በመታደግ በ2013 በጀት ዓመት የተገኘው ውጤት የሚያበረታታና በቀጣዩም ዓመት የተሸለ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ከፍተኛ ርብርብ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡
የኢኢግልድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ክብርት ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በስነ ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ድርጅቱ ባለፉት ዓመታት ካለፈባቸው የተወሳሰቡ የአሰራር፣ የአደረጃጀት፣ የግብዓት፣ የብልሹ አሰራር፣የቡድንተኝነት፣ የአሰራር እና አሳተፊነት ችግሮች ተወጥቶ አሁን የሚገኝበት ደረጃ ለመድረስ እልህ አስጨራሽ ችግሮች እንዳጋጠሟቸው በዝርዝር አመልክተው የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የድርጅቱ የስራ አመራር ቦርድ እና የድርጅቱ አመራሮች ስትራቴጂክ ውሳኔዎችን በመወሰን በአሁኑ ወቅት ችግሩን ተወጥተው በ2013 በጀት ዓመት በድርጅቱ ታሪክ ተገኝቶ የማይታወቀውን 96.7 በመቶ እቅድ አፈጻጸም እንደተመዘገበ አመልክተዋል፡፡
በመጨረሻም በዚህ ዓመት የተገኘውን ውጤት ምክንያት በማድረግ ይህንን ውጤት ላስመዘገቡና ለተገኘውም ውጤት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የበላይ ሃላፊዎች፣የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች፣ እጅግ ባነሰ ደሞዝ ድርጅቱን ድርጅቴ ብለው 25 እና ከዚያ በላይ ላገለገሉ ሠራተኞች እንዲሁም በክብር በጡረታ ለተገለሉ ሠራተኞች ይህ የእውቅና መርሃግብር እንደተዘጋጀ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በአገራችን የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ያለባቸውን የግብዓት አቅርቦት ችግር ለመፍታት በዋናነት በኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት ስራ ላይ ተሰማራ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡