የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት 2 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ድጋፍ ለሃገር መከላከያ ሠራዊት ሰጠ::

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) Receives Platinum Level Award
10/10/2025

Managers and experts of Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) participated on training held at the African Leadership Excellence Academy
25/09/2025

EIIDE Yarn Processing Center staffs conducted field visits
23/09/2025

EIIDE leaders and employees celebrated the completion of the Grand Renaissance Dam and annual workers' day
09/09/2025

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise (EIIDE) highlighted for strong performance for the 2024/25 budget year
27/08/2025

Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025

Nine-month Performance Review Session Highlights Considerable Achievements
21/04/2025

EIIDE leaders and employees celebrated International Women's Day.
17/03/2025

EIIDE conducted Eight-month plan performance review
17/03/2025

Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given
11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025

Financial and Audit Report
25/10/2023

Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE
26/12/2024

Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction
02/12/2024

EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year
23/10/2024

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding
23/10/2024

A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs
14/10/2024

Congratulations !!
11/10/2024

EIIDE awarded its management and employees for the successful performance of the 2023/24 fiscal year
26/08/2024

EIIDE became the highest awardee of the Abyssinian Industrial Award
22/07/2024
የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮች 2 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ደረቅ ራሽንና ቁሳቁሶችን ህዳር 26 ቀን 2014 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ከተማ በመገኘት ለሃገር መከላከያ ሠራዊት አስረከቡ፡፡
የኢኢግልድ ዋና ስራ አሰፈጻሚ ክብርት ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት ድርጅቱ ባለፉት ዓመታት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት እና በተለያየዩ ጊዜያት በተፈጠሩ ማህበራዊ ቀወሶች 15 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን የአሁኑን ድጋፍ የተለየ የሚደርገው ከዚህ በፊት ተደረገውን ድጋፍ ሳይጨምር የድርጅቱ አመራሮችና ሠራተኞች የአንድ ወር ደሞዛቸውን በመልቀቅ ብር 5.5 ሚሊዮን የሚጠጋ ድጋፍ ማበርከታቸው እንደሆነ አመልክተዋል፡፡
አያይዘውም ከድርጅቱ አመራሮችና ሠራተኞች ከተሰጠው ድጋፍ ውስጥ ባለፈው ሣምንት በወረኢሉ ግንባር በአካል በመገኘት 1.6 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ደረቅ ራሽንና ቁሳቁሶች የበረከቱ እንደሆነ ገልጸው በአሁኑ ወቅትም በደብረብርሃን ከተማ በአካል በመገኘት 2 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ድጋፎችን ለሠራዊቱ ማቅረባቸውን አብራርተዋል፡፡
በማጠቃለያቸውም በአገራችን የጦርነት ታሪክ ባንዳዎች በተለያዩ ጊዜያት እንደነበሩ ነገር ግን ሁልጊዜም እንደሚያፍሩና ኢትዮጵያም እንደምታሸንፍ አመልክተዋል፡፡
የግንባሩ ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪና የመከላከያ ሚኒስቴር ተወካይ ድጋፉን በተረከቡበት ወቅት እንደገለጹት ከራስ በፊት ህዝብና ሀገር ማስጠበቅን ዓላማ በማድረግ እየሠራ የሚገኘው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያን ለማዋረድና ለማፍረስ የመጣውን ጁንታ በማርበድበድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሠራዊቱም ይህንን ዓላማውን ለማስፈጸም የሚተማመነው ደጀን ህዝብ ደግሞ ሃብት በማሰባሰብና በአካልም ሆነ በተለያየ መልክ የሚያደርገው ድጋፍ ለሠራዊቱ ከፍተኛ አቅምና ጉልበት እንዲሁም የድል መነሻና መዳረሻ ሆኗቸዋል፡፡
ይህንንም ህዝባዊ ድጋፍ መሠረት በማድረግ በወረራ የተያዙትን ስፍራዎች በማስለቀቅ ተጨማሪ ድሎችን ለማብሰር የመከላከያ ሠራዊቱ ሌት ተቀን እየሰራ እንደሚገኝም የኮማንድ ፖስቱ ዋና አስተባባሪ አመልክተዋል፡፡
የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በአገሪቱ ባሉት ከ80 በላይ ቅርንጫፎች ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ግብዓት የሚያቀርብና የኢንዱስትሪ ውጤቶችና መሠረታዊ ሸቀጦች የሚያሰራጭ የመንግስት የልማት ድርጅት ሲሆን በአሁኑ ወቅት ጁንታው እያካሄደ በሚገኘው ጥቃት 12 የሽያጭ ቅርንጨፎቹ ሙሉ በሙሉ በመዘረፋቸው ከ500 ሚሊዮን ብር በለ ኪሳራ ደርሶበታል፡፡