ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ

18/01/2023

አርአያነት ያለው ተግባር

14/09/2022

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፍጆታ ምርቶች መሸጫ ዋጋ

09/09/2022

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ

29/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ

07/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ9ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ ምርትና አገልግሎቱን አስተዋወቀ

11/02/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ብር 265 ሚሊዮን የተጣራ ትርፍ ማግኘቱ ተገለጸ

04/02/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ

12/08/2022

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት የሚያቀርቡ አካላት ከህገወጥ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ጥሪ ቀረበ::

02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አምስት ወራት አፈጻጸሙን ገመገመ::

02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት 2 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ድጋፍ ለሃገር መከላከያ ሠራዊት ሰጠ::

02/09/2021

የኢኢግልድ አመራሮች በወረኢሉ ግንባር በመገኘት ለመከላከያ ሠራዊት ድጋፍ አበረከቱ::

02/09/2021

ኢኢግልድ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ

02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ነጩ ፖስታ ለነጩ ቤተመንግስት መርሃ ግብርን አካሄዱ

02/09/2021

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ የግንባታ የስምምነት ውል ተፈራረመ፡፡

02/09/2021

ከውጪ አገር ከተገዛው ዘይት 5.8 ሚሊየን ሊትር መግባቱ ተገለፀ።

02/09/2021

ኢኢግልድ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ሰጠ::

02/09/2021

ኢኢግልድ ለመንግስትና የግል ድርጅቶች ሠራተኞች የስንዴ ዱቄት በተመጣጣኝ ዋጋ አቀረበ

02/09/2021

ኢኢግልድ በየወሩ 52,080 ኩንታል የኢንዱስትሪ ጨው ለቆዳ ፋብሪካዎች ለማቅረብ የግዢ ውል ተፈራረመ

02/09/2021

ኢኢግልድ ከ2.7 ቢሊዮን ብር በላይ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችና ውጤቶችን አቀረበ

02/09/2021

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 21 results.

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት የሚያቀርቡ አካላት ከህገወጥ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ጥሪ ቀረበ::

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት በማቅረብ የህብረተሰቡን ጤና አደጋ ላይ መጣል ህገወጥ ተግባር መሆኑንና በዚህ ህገወጥ ተግባር የተሠማሩ አካላት ከዚህ ተግባራቸው እንዲታቀቡ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት እና የንግድ ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ከተማ ኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል በጥሬ ጨው አቅርቦት፣ ግብዓትና ሥርጭት ላይ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ታህሳስ 21 ቀን 2014 ዓ.ም አሳሰቡ፡፡

የኢግልድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በዚሁ መድረክ ላይ እንዳመላከቱት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ለአምራች ኢንዱስትሪዎቻችን የኢንዱስትሪ ጨው በብቸኝነት እንዲያቀርብ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተሠጠው ኃላፊነት መሠረት ወደ ሥራ ከገባ በኋላ በርካታ ችግሮችና ውጣ ውረዶችን በመጋፈጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡

አያይዘውም በኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት ሒደት ምርቱ ለማን፣ መቼ እንዴት ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚቻል የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት እያንዳንዱ የቆዳ ፋብሪካ ሰብሳቢና አቅራቢ ድርጅቶች እንዲሁም ጨው ለግብዓት የሚጠቀሙ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ምርቱን በአግባቡ በሥራ ላይ ለማዋላቸው ማረጋገጫ እንዲቀርብ የአሠራር ሥርዓት ተዘርግቶ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ጉዳዩ በንግድና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚ/ር እና በሌሎች ተቆጣጣሪና ክትትል በሚያካሂዱ ባለድርሻ አካላት የሚጣራ ጉዳይ ሆኖ ምንጩ ከየት እንደሆነ ያልታወቀ በአዮዲን ያልበለጸገ ጨው ለህብረተሰቡ ለምግብነት ገበያ ላይ እየቀረበ እንደሚኝ የገለጹት ወ/ሮ የሺመቤት ይህ ህገወጥ ተግባር ከየትና በማን እየተከናወነ እንደሚገኝና አፋጣኝ መፍትሄ እንደሚያስፈልገውም አመልክተዋል፡፡

በተጨማሪ የኢኢግልድን ምስል በማጠልሸት የራሳቸውን የምግብ ጨው አምራች ድርጅቶቻቸውን ሀብት ለማካበትና የተሸለ ምሰል ለመገንባትና በተቃራኒው ደግሞ የኢንዱስትሪ ጨው በብቸኝነት ለአምራች ኢንዱስትሪዎችና ሌሎችም ተጓዳኝ ማህበራት የሚያቀርበውን ኢኢግልድን ከኢንዱስትሪ ጨው ንግድ ለማስወጣት የሚደረግ የሴራ አካል እንደሆነ በውይይቱ ላይ የተነሳ ሲሆን ኢኢግልድ በዚህ ዓይነት ሕገወጥ ተግባር ውስጥ ስሙ ሊነሳ እንደማይገባ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡

በማጠቃለያም እየተካሔደ ያለው በአዮዲን ያልበለጸገ የምግብ ጨው ሥርጭት የህብረተሰቡን ጤና በእጅጉ የሚጐዳ በመሆኑ በዚህ ተግባር የተሠማሩ ሕገወጥ አካላትን በሚመለከታቸው ተቆጣጣሪ የመንግሥት ተቋማት ክትትል በማድረግ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝና በቀጣይም ክትትሉ፣ ቁጥጥሩና የሚወሰደውም ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በምክክር መድረኩ ላይ ተሳታፊ የነበሩ የንግድና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር፣ የሚመለከታቸው ባለድርሻና ተቆጣጣሪ መ/ቤቶች ኃላፊዎች አጽንኦት በመስጠት አሳስበዋል፡፡

በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ በኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት፣ ስርጭትና ግብይት ዙሪያ አቶ ዮናታን ሲሳይ በኢኢግልድ የግብዓት ግዢና ሽያጭ ዘርፍ የቃሊቲ ዲስትሪክት ሃላፊ አጭር ጥናታዊ ጽሁፍ ለተካሄደው ውይይት በመነሻነት አቅርበዋል፡፡

በውይይት መድረኩ በቆዳ ዘርፍ የተሰማሩ አምራቾች፣ የቆዳ ኢንስቲትዩት፣ የንግድ ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የምግብና መድሃኒት አስተዳደር ባለሥልጣንና ሌሎችም ጉዳዩ በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡