ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ
Training on procurement performance guidelines and change management has been given
10/11/2025
EIIDE's first quarter performance was announced as successful.
20/10/2025
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) Receives Platinum Level Award
10/10/2025
Managers and experts of Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) participated on training held at the African Leadership Excellence Academy
25/09/2025
EIIDE Yarn Processing Center staffs conducted field visits
23/09/2025
EIIDE leaders and employees celebrated the completion of the Grand Renaissance Dam and annual workers' day
09/09/2025
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise (EIIDE) highlighted for strong performance for the 2024/25 budget year
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
Nine-month Performance Review Session Highlights Considerable Achievements
21/04/2025
EIIDE leaders and employees celebrated International Women's Day.
17/03/2025
EIIDE conducted Eight-month plan performance review
17/03/2025
Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
Financial and Audit Report
25/10/2023
Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE
26/12/2024
Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction
02/12/2024
EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year
23/10/2024
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding
23/10/2024
A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs
14/10/2024
Congratulations !!
11/10/2024
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢኢግልድ) አመራሮችና ሠራተኞች ድርጅቱ በ2 ቢሊዮን ብር እያስገነባ ያለው የዋና መ/ቤት ህንጻና ግንባታቸው የተጠናቀቁ 48 ለንግድ ሥራ የሚያገለግሉ ሱቆች ጉብኝት ጥር 9 ቀን 2015 ዓ.ም አካሄዱ፡፡
በአገራችን የተካሄደውን ለውጥ ተከትሎ ኢኢግልድ ውስጥ የሚታዩትን የአሰራርና አፈጻጸም እንዲሁም የመልካም አስተዳደርና የሙስና ችግሮች ለመፍታት በተወሰደው እርምጃ የአመራሮች ለውጥ በማካሄድና የተለያዩ የሪፎርም ሥራዎች በማከናወን ላይ የሚገኙ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘ በተጨባጭ ውጤት የተገኘባቸው ሁለት ፕሮጀክቶች ተመርጠው በድርጅቱ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች እንዲሁም ሠራተኞች እንዲጎበኙ ተደርገዋል፡፡
ድርጅቱ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ መድቦ እያስገነባ የሚገኘው ባለ 18 ፎቅ የዋና መ/ቤት ህንጻ አንዱ ሲሆን ህንጻው ከዋና መ/ቤት ጽ/ቤት ባሻገር የተለያዩ አገልግሎት የሚሰጡ በተለይም ለባንክ፣ ሱፐር ከርኬት፣ ለጂምና ለተለያዩ አገልግሎቶች ሊውል ታቅዶ ግንባታው እተካሄደ እንደሆነ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል፡፡
ከሜክሲኮ አደባባይ ዝቅ ብሎ አፍሪካ ፍብረት አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው ይህ ህንጻ በሁለት ዓመታት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ 46 በመቶ እንደተከናወነ እስከ 2015 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ የግንባታው 80 በመቶ እንደሚጠናቀቅ፤ ፕሮጀክቱ በዕቅዱ መሠረት እየተካሄደ እንደሚገኝ የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት አመልክቷል፡፡
በአመራሮችና ሠራተኞች ጉብኝት የተካሄደበት ሌላው ፕሮጀክት ግንባታቸው የተጠናቀቁና ለአገልግሎት ዝግጁ የተደረጉት በቃሊቲ ማዕከላዊ ዲስትሪክት የሚገኙት 48 ሱቆች ሲሆኑ ከዚህም በተጨማሪ ለቆዳ ውጤቶች ማምረቻ እንዲያገለግሉ የተገነቡትም ሼዶች በዚሁ ወቅት ጉብኝት ተካተዋል፡፡
በቀጣይም ድርጅቱ በቆዳ ውጤቶች ላይ በማተኮር በቃሊቲ ማዕከላዊ ዲስትሪክት ባለ 4 ፎቅ ህንጻዎችን ለመገንባትና በቆዳ ውጤቶች ኤክስፖርት ንግድ ላይ ለመሰማራት እየሰራ እንደሚገኝም በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል፡፡
የኢኢግል ድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት ድርጅቱ የነበሩበትን የመልካም አስተዳደር ፣ የሙስና፣ ወቅቱን የዋጀ ዘመናዊ የአሰራርና የአፈጻጸም ችግሮች በመለየት የሪፎርም ስራዎች ተጠናክሮ እንዲሰራ በመደረጉ አሁን ለተገኙት ውጤቶች አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን አመልክተዋል፡፡
በተካሄዱትም የሪፎርም ስራዎች ድርጅቱን የሚመጥን መዋቅር በማስጠናት እንዲተገበር የተደረገ መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ የሺመቤት ቀድሞ የነበሩ መመሪያዎች እንዲሻሻሉና 10 አዳዲስ መመሪያዎች ተዘጋጅተው በድርጅቱ ስራ አመራር ቦርድ እንዲጸድቁ ተደርገው ወደስራ እንደተገባ፤ አሰራርን ለማዘመን ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት የመሟላት ስራዎች እንደተከናወነ፤ የካፒታል ኢንቨስትመንት ስራዎችን በማጠናከር የድርጅቱን የሎጀስቲክስ አቅም ለመገንባት 5 የደረቅ ጭነት ተሳቢ ፣ 6 የመስክና 7 የከተማ ተሸከርካሪዎች ግዢ ተከናውኖ ወደ ስራ እንዲገቡ እንደተደረገ አመልክተዋል፡፡
በተጨማሪም 500 ኩንታል የመጫን አቅም ያላቸው 24 ተሳቢ የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪዎች ግዢ የተካሄደ ሲሆን የተለያዩ ውጪያዊ ችግሮችን ቢኖሩም በቀጣዩ ሶስት ወራት ውስጥ ርክክብ የካሄዳል ተብሎ እንደሚጠበቅና በአጠቃላይ ከ230 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገ አመልክተዋል፡፡
በማጠቃለያም የድርጅቱ ሠራተኖች እየተከናወኑ ያሉትን የለውጥ ስራዎችና የተገኙትን ውጤቶች እንዲሁም የታቀዱትን ዓበይት ተግባራት ግምት ውስጥ በማስገባት የድርጅቱ አመራሮችና ሠራተኞች ሙሉ አቅማቸውንና ዕወቀታቸውን ድርጅቱን ለማሳደግ እንዲያውሉ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አሳስበዋል፡፡



