ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ
Members of the Standing Committee on Trade and Industry of the House of peoples Representatives visited EIIDE
29/01/2024
EIIDE conducted Six month Plan performance Evaluation
17/01/2024
Sales Announcement
27/11/2023
Announcement regarding the supply of premix needed to enrich cooking oil with vitamins
06/11/2023
EIIDE evaluates its first quarter plan performance at Elilly Hotel
06/11/2023
Notice
25/10/2023
EIIDE donated 4.2 million birr sanitary pad
17/10/2023
EIIDE offered 16.5 million liters of edible oil at a reasonable price
14/09/2023
EIIDE conducted an evaluation of the of the 2022/23 fiscal year plan and the next year's plan of the enterprise
23/08/2023
Members of the Management Board visited projects of EIIDE
31/07/2023
Managers and Employees of EIIDE Conducted Green Legacy
27/07/2023
EIIDE has launched a women's workers forum
20/07/2023
ኢኢግልድ የ2015 በጀት ዓመት የስምንት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
11/04/2023
ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ
23/03/2023
ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ
18/01/2023
አርአያነት ያለው ተግባር
14/09/2022
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፍጆታ ምርቶች መሸጫ ዋጋ
09/09/2022
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ
29/08/2022
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ
07/08/2022
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ9ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ ምርትና አገልግሎቱን አስተዋወቀ
09/02/2022
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢኢግልድ) አመራሮችና ሠራተኞች ድርጅቱ በ2 ቢሊዮን ብር እያስገነባ ያለው የዋና መ/ቤት ህንጻና ግንባታቸው የተጠናቀቁ 48 ለንግድ ሥራ የሚያገለግሉ ሱቆች ጉብኝት ጥር 9 ቀን 2015 ዓ.ም አካሄዱ፡፡
በአገራችን የተካሄደውን ለውጥ ተከትሎ ኢኢግልድ ውስጥ የሚታዩትን የአሰራርና አፈጻጸም እንዲሁም የመልካም አስተዳደርና የሙስና ችግሮች ለመፍታት በተወሰደው እርምጃ የአመራሮች ለውጥ በማካሄድና የተለያዩ የሪፎርም ሥራዎች በማከናወን ላይ የሚገኙ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘ በተጨባጭ ውጤት የተገኘባቸው ሁለት ፕሮጀክቶች ተመርጠው በድርጅቱ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች እንዲሁም ሠራተኞች እንዲጎበኙ ተደርገዋል፡፡
ድርጅቱ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ መድቦ እያስገነባ የሚገኘው ባለ 18 ፎቅ የዋና መ/ቤት ህንጻ አንዱ ሲሆን ህንጻው ከዋና መ/ቤት ጽ/ቤት ባሻገር የተለያዩ አገልግሎት የሚሰጡ በተለይም ለባንክ፣ ሱፐር ከርኬት፣ ለጂምና ለተለያዩ አገልግሎቶች ሊውል ታቅዶ ግንባታው እተካሄደ እንደሆነ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል፡፡
ከሜክሲኮ አደባባይ ዝቅ ብሎ አፍሪካ ፍብረት አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው ይህ ህንጻ በሁለት ዓመታት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ 46 በመቶ እንደተከናወነ እስከ 2015 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ የግንባታው 80 በመቶ እንደሚጠናቀቅ፤ ፕሮጀክቱ በዕቅዱ መሠረት እየተካሄደ እንደሚገኝ የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት አመልክቷል፡፡
በአመራሮችና ሠራተኞች ጉብኝት የተካሄደበት ሌላው ፕሮጀክት ግንባታቸው የተጠናቀቁና ለአገልግሎት ዝግጁ የተደረጉት በቃሊቲ ማዕከላዊ ዲስትሪክት የሚገኙት 48 ሱቆች ሲሆኑ ከዚህም በተጨማሪ ለቆዳ ውጤቶች ማምረቻ እንዲያገለግሉ የተገነቡትም ሼዶች በዚሁ ወቅት ጉብኝት ተካተዋል፡፡
በቀጣይም ድርጅቱ በቆዳ ውጤቶች ላይ በማተኮር በቃሊቲ ማዕከላዊ ዲስትሪክት ባለ 4 ፎቅ ህንጻዎችን ለመገንባትና በቆዳ ውጤቶች ኤክስፖርት ንግድ ላይ ለመሰማራት እየሰራ እንደሚገኝም በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል፡፡
የኢኢግል ድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት ድርጅቱ የነበሩበትን የመልካም አስተዳደር ፣ የሙስና፣ ወቅቱን የዋጀ ዘመናዊ የአሰራርና የአፈጻጸም ችግሮች በመለየት የሪፎርም ስራዎች ተጠናክሮ እንዲሰራ በመደረጉ አሁን ለተገኙት ውጤቶች አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን አመልክተዋል፡፡
በተካሄዱትም የሪፎርም ስራዎች ድርጅቱን የሚመጥን መዋቅር በማስጠናት እንዲተገበር የተደረገ መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ የሺመቤት ቀድሞ የነበሩ መመሪያዎች እንዲሻሻሉና 10 አዳዲስ መመሪያዎች ተዘጋጅተው በድርጅቱ ስራ አመራር ቦርድ እንዲጸድቁ ተደርገው ወደስራ እንደተገባ፤ አሰራርን ለማዘመን ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት የመሟላት ስራዎች እንደተከናወነ፤ የካፒታል ኢንቨስትመንት ስራዎችን በማጠናከር የድርጅቱን የሎጀስቲክስ አቅም ለመገንባት 5 የደረቅ ጭነት ተሳቢ ፣ 6 የመስክና 7 የከተማ ተሸከርካሪዎች ግዢ ተከናውኖ ወደ ስራ እንዲገቡ እንደተደረገ አመልክተዋል፡፡
በተጨማሪም 500 ኩንታል የመጫን አቅም ያላቸው 24 ተሳቢ የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪዎች ግዢ የተካሄደ ሲሆን የተለያዩ ውጪያዊ ችግሮችን ቢኖሩም በቀጣዩ ሶስት ወራት ውስጥ ርክክብ የካሄዳል ተብሎ እንደሚጠበቅና በአጠቃላይ ከ230 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገ አመልክተዋል፡፡
በማጠቃለያም የድርጅቱ ሠራተኖች እየተከናወኑ ያሉትን የለውጥ ስራዎችና የተገኙትን ውጤቶች እንዲሁም የታቀዱትን ዓበይት ተግባራት ግምት ውስጥ በማስገባት የድርጅቱ አመራሮችና ሠራተኞች ሙሉ አቅማቸውንና ዕወቀታቸውን ድርጅቱን ለማሳደግ እንዲያውሉ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አሳስበዋል፡፡