ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ
Financial and Audit Report 2023/24
25/03/2026
Financial and Audit Report 2022/23
25/03/2026
ኢኢግልድ የ2018 በጀት ዓመት 8 ወራት አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
16/03/2026
ሙያን መሠረት አድርጎ የሚሰጥ ተከታታይ ስልጠና ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ
09/03/2026
በስድስት ወራት አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች ዕውቅና ተሰጠ
27/01/2026
በመንግሥት የልማት ድርጀቶች የግዢ አፈጻጸም መመሪያና በለውጥ ሥራዎች ላይ ሲሰጥ የነበረዉ ሥልጠና ተጠናቀቀ
10/11/2025
የኢኢግልድ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ
20/10/2025
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ሆነ
10/10/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የአመራሮች ስልጠና በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተካሔደ
25/09/2025
የኢኢግልድ የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች በፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ
23/09/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የሠራተኞችን ዓመታዊ በዓል አከበሩ
09/09/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) በበጀት ዓመቱ ጠንካራ አፈጻጸም አስመዘገበ
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
በአገራዊና ተቋማዊ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሔደ
21/04/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ
17/03/2025
የኢኢግልድ ሽያጭ ቅርንጫፎችና ዲስትሪክቶች የስምንት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
17/03/2025
በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
ማስታወቂያ
25/10/2023
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ
26/12/2024
ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ጋር በተያያዘ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ 33 የድርጅቱ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች በቢሻፍቱ ከተማ ከመጋቢት 4-8 2015 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
ለአምስት ቀናት የተሰጠው ስልጠና የድርጅቱን የአሰራር ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመጣጣኝና ዘመናዊ በማድረግ ኢኢግልድን ተወዳዳሪና ውጤታማ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አማካሪነት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራው ክትትል እንደሚከሄድም ታውቋል፡፡
ከዚህ ሥልጠና ቀደም ባሉት ጊዜያት ከጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት አንጻር በድርጅታችን ዋናው መስሪያ ቤት እና በዲስትሪክቶች በመገኘት መረጃዎችን በማሰባሰብ፣ ትንተና በማካሄድ የአሰራር ሥርዓት ክፍተት (Gap assessment) ተለይቶ የጥናት ሪፖርቱ ለማኔጅመንት የቀረበ ሲሆን ስለ ጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ገለጻ ተደርጎ በድርጅታችን ማኔጅመንቱ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በመሆኑም ለጥራት ስራ አመራር ስርዓቱ ልማትና ትግበራ የጥራት አስተባባሪ የተመደበ ሲሆን የአሰራር ስርዓቱን ለመተግበር እንዲቻል ከሁሉም የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ 33 አባላትን ያካተተ ግብረ-ኃይል ተመርጦ ወደ ስልጠናው ተገብቷል፡፡
በቀጣይም በተመሳሳይ ዘርፍ የተሰማሩ ሆነው የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ተግባራዊ ካደረጉ ድርጅቶች የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ እንዲሁም የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ትግበራ ዕውን ለማድረግ የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን፣ ፕሮሲጀር ማንዋሎችን፣ የሥራ መመሪያዎች፣ ቅጾችን እና ሌሎች ዶክመንቶችን በመለየት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ለመተግበር የሚያስፈልጉ ዶክመንቶች እንዲዘጋጁ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡
ከዚህ አንጻር በየሥራ ክፍሎች መመሪያዎች፣ ፕሮሲጀር ማንዋሎችን፣ የሥራ መመሪያዎች፣ ቅጾችን እና ሌሎች ዶክመንቶችን በመለየት በጥራት ሥራ አመራር አሠራር ሥርዓት መርህ መሠረት ተግባራዊ በማድረግ ድርጅታችን ተወዳዳሪና ውጤታማ በማድረግ፤ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን እንዲሁም የገበያ ማረጋጋት ሥራን ውጤታማ በሆነ አሰራር በመምራት ድርጅቱን ተወዳዳሪ፣ ውጤታማ እና ትርፋማ በማድረግ ለአገራችን ኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን ሚና የሚወጣ ተቋም ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡