Financial and Audit Report 2020/21

28/01/2025

ማስታወቂያ

25/10/2023

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ

26/12/2024

የኢኢግልድ የበላይ አመራሮችና ሃላፊዎች በግንባታ ላይ የሚገኘውን ዋና መ/ቤት ህንፃ ጎበኙ

02/12/2024

ኢኢግልድ በበጀት ዓመቱ አራት ወራት የዕቅዱን 96 በመቶ ማከናወኑ ተገለጸ

23/10/2024

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅትና የኢትዮጵያ ፖስታ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረሙ

23/10/2024

በኢንዱስትሪ ግብዓቶች አቅርቦት ተግዳሮቶችና መፍትሄ ላይ ውይይት ተካሄደ

14/10/2024

እንኳን ደስ አላችሁ!!!

11/10/2024

ኢኢግልድ ላገኘው የ2016 በጀት ዓመት ስኬታማ አፈጻጸም ለአመራሮቹና ሠራተኞቹ እውቅና ሰጠ

26/08/2024

ኢኢግልድ የአቢሲኒያ ኢንዱስትሪዎች ሽልማት ከፍተኛ ተሸላሚ ሆነ

22/07/2024

የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሃላፊዎች የችግኝ ተከላ አካሄዱ

20/07/2024

የማዕከላዊና የምዕራብ ዲስትሪክት ጽ/ቤቶች አስር ወራት ዕቅድ አፈጻጸምና 2017 የኮርፖሬት ዕቅድ ግምገማ ተካሄደ

20/05/2024

ኢኢግልድ በስትራቴጂክ ዕቅዱና በአሰራር መመሪያዎች ረቂቅ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን ግምገማ አጠናቀቀ

13/05/2024

ኢኢግልድ ስትራቴጂክ ዕቅዱና ሌሎችም የአሰራር ስርዓቶቹን እየገመገመ ይገኛል

10/05/2024

ኢኢግልድ በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ ተሳተፈ

09/05/2024

ኢኢግልድ 10ኛው አገር ዓቀፍ የሕብረት ሥራ ማሕበራት ኤግዚቢሽንና ባዛር ተሳተፈ

15/02/2024

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በኢኢግልድ ጉብኝት አካሄዱ

29/01/2024

የአመራሮችና የባለሙያዎች ቅንጅትና የስራ ትጋት ለድርጅቱን አፈጻጸም ውጤታማነት ሚና እንደሚኖረው ተገለጸ

17/01/2024

ማስታወቂያ

27/11/2023

የምግብ ዘይት በቫይታሚን ለማበልጸግ የሚያስፈልገውን የፕሪሚክስ አቅርቦትን አስመልክቶ የወጣ ማስታወቂያ

06/11/2023

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 49 results.

ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ

ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ጋር በተያያዘ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ 33 የድርጅቱ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች በቢሻፍቱ ከተማ ከመጋቢት 4-8 2015 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

ለአምስት ቀናት የተሰጠው ስልጠና የድርጅቱን የአሰራር ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመጣጣኝና ዘመናዊ በማድረግ ኢኢግልድን ተወዳዳሪና ውጤታማ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አማካሪነት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራው ክትትል እንደሚከሄድም ታውቋል፡፡

ከዚህ ሥልጠና ቀደም ባሉት ጊዜያት ከጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት አንጻር በድርጅታችን ዋናው መስሪያ ቤት እና በዲስትሪክቶች በመገኘት መረጃዎችን በማሰባሰብ፣ ትንተና በማካሄድ የአሰራር ሥርዓት ክፍተት (Gap assessment) ተለይቶ የጥናት ሪፖርቱ ለማኔጅመንት የቀረበ ሲሆን ስለ ጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ገለጻ ተደርጎ በድርጅታችን ማኔጅመንቱ ውይይት ተካሂዷል፡፡

በመሆኑም ለጥራት ስራ አመራር ስርዓቱ ልማትና ትግበራ የጥራት አስተባባሪ የተመደበ ሲሆን የአሰራር ስርዓቱን ለመተግበር እንዲቻል ከሁሉም የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ 33 አባላትን ያካተተ ግብረ-ኃይል ተመርጦ ወደ ስልጠናው ተገብቷል፡፡

በቀጣይም በተመሳሳይ ዘርፍ የተሰማሩ ሆነው የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ተግባራዊ ካደረጉ ድርጅቶች የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ እንዲሁም የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ትግበራ ዕውን ለማድረግ የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን፣ ፕሮሲጀር ማንዋሎችን፣ የሥራ መመሪያዎች፣ ቅጾችን እና ሌሎች ዶክመንቶችን በመለየት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ለመተግበር የሚያስፈልጉ ዶክመንቶች እንዲዘጋጁ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡

ከዚህ አንጻር በየሥራ ክፍሎች መመሪያዎች፣ ፕሮሲጀር ማንዋሎችን፣ የሥራ መመሪያዎች፣ ቅጾችን እና ሌሎች ዶክመንቶችን በመለየት በጥራት ሥራ አመራር አሠራር ሥርዓት መርህ መሠረት ተግባራዊ በማድረግ ድርጅታችን ተወዳዳሪና ውጤታማ በማድረግ፤ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን እንዲሁም የገበያ ማረጋጋት ሥራን ውጤታማ በሆነ አሰራር በመምራት ድርጅቱን ተወዳዳሪ፣ ውጤታማ እና ትርፋማ በማድረግ ለአገራችን ኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን ሚና የሚወጣ ተቋም ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡