ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ
ኢኢግልድ ስትራቴጂክ ዕቅዱና ሌሎችም የአሰራር ስርዓቶቹን እየገመገመ ይገኛል
10/05/2024
ኢኢግልድ ስትራቴጂክ ዕቅዱና ሌሎችም የአሰራር ስርዓቶቹን እየገመገመ ይገኛል
10/05/2024
ኢኢግልድ በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ ተሳተፈ
09/05/2024
ኢኢግልድ 10ኛው አገር ዓቀፍ የሕብረት ሥራ ማሕበራት ኤግዚቢሽንና ባዛር ተሳተፈ
15/02/2024
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በኢኢግልድ ጉብኝት አካሄዱ
29/01/2024
የአመራሮችና የባለሙያዎች ቅንጅትና የስራ ትጋት ለድርጅቱን አፈጻጸም ውጤታማነት ሚና እንደሚኖረው ተገለጸ
17/01/2024
ማስታወቂያ
27/11/2023
የምግብ ዘይት በቫይታሚን ለማበልጸግ የሚያስፈልገውን የፕሪሚክስ አቅርቦትን አስመልክቶ የወጣ ማስታወቂያ
06/11/2023
ኢኢግልድ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ገመገመ
06/11/2023
ማስታወቂያ
25/10/2023
ኢኢግልድ የ4.2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበረከተ
17/10/2023
ኢኢግልድ የ16.5 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት በተመጣጣኝ ዋጋ አቀረበ
14/09/2023
ኢኢግልድ የዲስትሪክቶችን የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ግምገማ አካሄደ
23/08/2023
የኢኢግልድ ሥራ አመራር ቦርድ አባላት በግንባታ ላይ የሚገኙና ግንባታቸው የተጠናቀቁ ፕሮክቶችን ጎበኙ
31/07/2023
ኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አካሄዱ
27/07/2023
የኢኢግልድ ሴት ሠራተኞች ፎረም ተመሰረተ
20/07/2023
ኢኢግልድ የ2015 በጀት ዓመት የስምንት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
11/04/2023
ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ
23/03/2023
ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ
18/01/2023
አርአያነት ያለው ተግባር
14/09/2022
ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ጋር በተያያዘ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ 33 የድርጅቱ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች በቢሻፍቱ ከተማ ከመጋቢት 4-8 2015 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
ለአምስት ቀናት የተሰጠው ስልጠና የድርጅቱን የአሰራር ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመጣጣኝና ዘመናዊ በማድረግ ኢኢግልድን ተወዳዳሪና ውጤታማ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አማካሪነት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራው ክትትል እንደሚከሄድም ታውቋል፡፡
ከዚህ ሥልጠና ቀደም ባሉት ጊዜያት ከጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት አንጻር በድርጅታችን ዋናው መስሪያ ቤት እና በዲስትሪክቶች በመገኘት መረጃዎችን በማሰባሰብ፣ ትንተና በማካሄድ የአሰራር ሥርዓት ክፍተት (Gap assessment) ተለይቶ የጥናት ሪፖርቱ ለማኔጅመንት የቀረበ ሲሆን ስለ ጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ገለጻ ተደርጎ በድርጅታችን ማኔጅመንቱ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በመሆኑም ለጥራት ስራ አመራር ስርዓቱ ልማትና ትግበራ የጥራት አስተባባሪ የተመደበ ሲሆን የአሰራር ስርዓቱን ለመተግበር እንዲቻል ከሁሉም የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ 33 አባላትን ያካተተ ግብረ-ኃይል ተመርጦ ወደ ስልጠናው ተገብቷል፡፡
በቀጣይም በተመሳሳይ ዘርፍ የተሰማሩ ሆነው የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ተግባራዊ ካደረጉ ድርጅቶች የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ እንዲሁም የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ትግበራ ዕውን ለማድረግ የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን፣ ፕሮሲጀር ማንዋሎችን፣ የሥራ መመሪያዎች፣ ቅጾችን እና ሌሎች ዶክመንቶችን በመለየት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ለመተግበር የሚያስፈልጉ ዶክመንቶች እንዲዘጋጁ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡
ከዚህ አንጻር በየሥራ ክፍሎች መመሪያዎች፣ ፕሮሲጀር ማንዋሎችን፣ የሥራ መመሪያዎች፣ ቅጾችን እና ሌሎች ዶክመንቶችን በመለየት በጥራት ሥራ አመራር አሠራር ሥርዓት መርህ መሠረት ተግባራዊ በማድረግ ድርጅታችን ተወዳዳሪና ውጤታማ በማድረግ፤ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን እንዲሁም የገበያ ማረጋጋት ሥራን ውጤታማ በሆነ አሰራር በመምራት ድርጅቱን ተወዳዳሪ፣ ውጤታማ እና ትርፋማ በማድረግ ለአገራችን ኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን ሚና የሚወጣ ተቋም ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡