የኢኢግልድ የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች በፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ሆነ
10/10/2025

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የአመራሮች ስልጠና በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተካሔደ
25/09/2025

የኢኢግልድ የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች በፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ
23/09/2025

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የሠራተኞችን ዓመታዊ በዓል አከበሩ
09/09/2025

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) በበጀት ዓመቱ ጠንካራ አፈጻጸም አስመዘገበ
27/08/2025

Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025

በአገራዊና ተቋማዊ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሔደ
21/04/2025

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ
17/03/2025

የኢኢግልድ ሽያጭ ቅርንጫፎችና ዲስትሪክቶች የስምንት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
17/03/2025

በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025

ማስታወቂያ
25/10/2023

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ
26/12/2024

የኢኢግልድ የበላይ አመራሮችና ሃላፊዎች በግንባታ ላይ የሚገኘውን ዋና መ/ቤት ህንፃ ጎበኙ
02/12/2024

ኢኢግልድ በበጀት ዓመቱ አራት ወራት የዕቅዱን 96 በመቶ ማከናወኑ ተገለጸ
23/10/2024

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅትና የኢትዮጵያ ፖስታ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረሙ
23/10/2024

በኢንዱስትሪ ግብዓቶች አቅርቦት ተግዳሮቶችና መፍትሄ ላይ ውይይት ተካሄደ
14/10/2024

እንኳን ደስ አላችሁ!!!
11/10/2024

ኢኢግልድ ላገኘው የ2016 በጀት ዓመት ስኬታማ አፈጻጸም ለአመራሮቹና ሠራተኞቹ እውቅና ሰጠ
26/08/2024

ኢኢግልድ የአቢሲኒያ ኢንዱስትሪዎች ሽልማት ከፍተኛ ተሸላሚ ሆነ
22/07/2024
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢኢግልድ) ፈረንሳይ ለጋሲዮን በሚገኘው የሽያጭ ቅርንጫፉ በቅርቡ ያቋቋመውና ስራ ያስጀመረው የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች መስከረም 9 እና 10/2018 ዓ.ም በአልሳም እና ቡሉኮ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት እና ምልከታ አካሄዱ፡፡
የፕሮጀክት ጥናት ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ወ/ዮሐንስ እንደገለጹት ኢኢግልድ ፈረንሳይ ለጋሲዮን በሚገኘው የሽያጭ ቅርንጫፉ የክር ማጠንጠኛ ማዕከል አቋቁሞ የተጠነጠኑ ክሮችን ከፈትል እና ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች ገዝቶ ምርት በማምረት በማጠንጠን በሽመና ስራ ላይ ለተሰማሩ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች እና ኢንተርፕራይዞች ለገበያ እያቀረበ የሚገኝ ሲሆን የጉብኝቱ ዓላማም ማዕከሉ በቅርብ ቀን የተቋቋመ ከመሆኑ አንጻር በዘርፉ የካበተ ልምድ እና ተሞክሮ ካላቸው ተመሳሳይ ተቋማት ልምድ ወስደው የማምረት አቅማቸውን በማጎልበት በቀጣይ ማዕከሉን ምርት እና ምርታማነት ለማሳደግ ነው፡፡
በጉብኝቱ የተሳተፉት ሰራተኞች በሁለቱም ፋብሪካዎች የክር ማጠንጠኞ ክፍል በመገኘት ከምርት ግብዓት ዝግጅት ጀምሮ ምርት እስከሚመረትበት ደረጃ ፤ በእያንዳንዱ የምርት ሂደት የሚከናወኑ ተግባራቶችና የአመራረት ሂደቶች ፣ የምርት የጥራት አጠባበቅ ዘዴ፣ በምርት ጥራት አጠባበቅ ሂደት ላይ የሰራተኞቹ ሚና እና ድርሻ፤ የፋብሪካዎቹ የምርት የጥራት መለኪያ መስፈርቶች ፤ የፋብሪካ ሰራተኞች የሥራ ባህል እና ዲስፕሊን እንዲሁም በሌሎች ተጓዳኝ ጉዳዮች ላይ ሰራተኞቹ ግንዛቤ፤ ልምድ እና ተሞክሮ እንዱወስዱ ተደርጓል፡፡
በመስክ ጉብኝቱ የተሳተፉ ሰራተኞች እንደገለጹት ድርጅቱ ለማዕከሉ ሰራተኞች ትኩረት ሰጥቶ ይህን ጉብኝት ማዘጋጀቱ የስራ ተነሳሽነት የፈጠረላቸው ከመሆኑም በላይ ተጨማሪ ዕውቀት፣ ልምድ እና ግንዛቤ ያገኙበት እና ያገኙትንም ልምድ ተግባራዊ እንደሚያደርጉ ገልጸው እንደዚህ ዓይነት ፕሮግራሞች ቀጠይነት እንዲኖራቸው አስተያቶቻቸውን ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም በመስክ ጉብኝቱ የተገኙት ልምዶች እና ምርጥ ተሞክሮዎችን ተቀምረው ወደ ማዕከሉ በማስፋት ተግባራዊ የሚሆንበት ሁኔታ እንደሚመቻች የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ወ/ዮሐንስ ገልጸዋል፡፡