ኢኢግልድ የ2018 በጀት ዓመት 8 ወራት አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
Financial and Audit Report 2023/24
25/03/2026
Financial and Audit Report 2022/23
25/03/2026
ኢኢግልድ የ2018 በጀት ዓመት 8 ወራት አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
16/03/2026
ሙያን መሠረት አድርጎ የሚሰጥ ተከታታይ ስልጠና ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ
09/03/2026
በስድስት ወራት አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች ዕውቅና ተሰጠ
27/01/2026
በመንግሥት የልማት ድርጀቶች የግዢ አፈጻጸም መመሪያና በለውጥ ሥራዎች ላይ ሲሰጥ የነበረዉ ሥልጠና ተጠናቀቀ
10/11/2025
የኢኢግልድ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ
20/10/2025
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ሆነ
10/10/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የአመራሮች ስልጠና በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተካሔደ
25/09/2025
የኢኢግልድ የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች በፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ
23/09/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የሠራተኞችን ዓመታዊ በዓል አከበሩ
09/09/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) በበጀት ዓመቱ ጠንካራ አፈጻጸም አስመዘገበ
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
በአገራዊና ተቋማዊ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሔደ
21/04/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ
17/03/2025
የኢኢግልድ ሽያጭ ቅርንጫፎችና ዲስትሪክቶች የስምንት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
17/03/2025
በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
ማስታወቂያ
25/10/2023
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ
26/12/2024
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ2018 በጀት ዓመት ስምንት ወራት የተገኘው አበረታች አፈጻጸም ውጤት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባና በየእርከኑ የሚገኙ የዘርፎች፣ ዳይሬክቶሬቶች እና የዲስትሪክት ጽ/ቤቶች አመራሮች በቀሪው አራት ወራት በቁርጠኝነትና በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
የኢኢግልድ ተ/ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳዊት አዳነ ይህንን የገለጹት ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረውን የድርጅቱ የ2018 በጀት ዓመት የውይይትና የግምገማ መድረክ መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ማጠናቀቂያ ላይ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የዘርፎች፣ ዲስትሪክት ጽ/ቤቶችና ዳይሬክቶሬቶች አመራሮች እንዲሁም የድርጅቱ ባለሙያዎችና ሠራተኞች ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አመልክተው፤ ከዚህም ባሻገር የድርጅቱ ግዢና ሽያጭ አፈጻጸም፣ የድርጅቱን የፋይናንስ የአሰራር ሥርዓት ለማሻሻልና ለማዘመን እየተሰራ ያለው ሥራ፣ በድርጅቱ እየተተገበረ ያለው የኢንተርፕራይዝ ሀብት እቅድ/አስተዳደር(ERP) ትግበራ እና የድረጅቱን የ2016 በጀት ዓመት ሒሳብ በውጭ ኦዲተር ተጣርቶ ማረጋገጫ መገኘቱ በዋናነት በስኬት ሊነሱ የሚችሉ ሥራዎች እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡
አያይዘውም የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠልና የአሠራር ክፍተት የታየባቸውን ተግባራትና የስራ ክፍሎች እንዲሻሻሉ የድጋፍና ክትትል ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የአመራሮች ሚና ወሳኝ በመሆኑ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ፤ በቀሪዎቹ አራት ወራት በየእርከኑ የሚገኙ ባለሙያዎች በየሥራ ክፍላቸው የተሠጣቸውን ተግባርና ሃላፊነት በተገቢው መልኩ ሊወጡ እንደሚገባ ጨምረው አሳስበዋል፡፡
ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የድርጅቱ የስምንት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በቀሪዎቹ አራት ወራት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳከት የሁሉም የሥራ ክፍሎች በትኩረት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያቀርብና ኢንዱስትሪዎች ያመረቷቸውን የኢንዱስትሪ ውጤቶች በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያ የማረጋጋት ሥራዎችን የሚያከናውን የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡





