ሙያን መሠረት አድርጎ የሚሰጥ ተከታታይ ስልጠና ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ
Financial and Audit Report 2023/24
25/03/2026
Financial and Audit Report 2022/23
25/03/2026
ኢኢግልድ የ2018 በጀት ዓመት 8 ወራት አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
16/03/2026
ሙያን መሠረት አድርጎ የሚሰጥ ተከታታይ ስልጠና ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ
09/03/2026
በስድስት ወራት አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች ዕውቅና ተሰጠ
27/01/2026
በመንግሥት የልማት ድርጀቶች የግዢ አፈጻጸም መመሪያና በለውጥ ሥራዎች ላይ ሲሰጥ የነበረዉ ሥልጠና ተጠናቀቀ
10/11/2025
የኢኢግልድ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ
20/10/2025
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ሆነ
10/10/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የአመራሮች ስልጠና በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተካሔደ
25/09/2025
የኢኢግልድ የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች በፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ
23/09/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የሠራተኞችን ዓመታዊ በዓል አከበሩ
09/09/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) በበጀት ዓመቱ ጠንካራ አፈጻጸም አስመዘገበ
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
በአገራዊና ተቋማዊ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሔደ
21/04/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ
17/03/2025
የኢኢግልድ ሽያጭ ቅርንጫፎችና ዲስትሪክቶች የስምንት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
17/03/2025
በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
ማስታወቂያ
25/10/2023
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ
26/12/2024
የአሠራር ክፍተቶችን መሠረት አደርጎ የሚሰጥ ተከታታይ ሥልጠና በአፈጻጸም ወቅት ሊፈጠሩ የሚችሉ ችግሮችን በማስወገድ ስራዎችን እንደሚያሳልጥ ኢኢግልድ በአዳማ ከተማ ለሁለት ቀናት ባዘጋጀው ስልጠና የተሳተፉ የድርጅቱ ባለሙያዎች ገለጹ::
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ከየካቲት 28-29/2018 ዓ.ም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በድርጅቱ በስራ ላይ ካዋለው የኢንተርፕራይዝ ሐብት እቅድ/ አስተዳደር (ERP) ትግበራ ጋር በተያያዘ ባዘጋጀው የሁለት ቀናት ሥልጠና እየተሳተፉ የሚገኙ የፋይናንስና የሽያጭ ባለሙያዎች ናቸው፡፡
በሥልጠናው የተሳተፉ ባለሙያዎች በአፈጻጸም ወቅት የገጠሟቸው ችግሮችና የአሠራር ክፍቶችን አቅርበው በድርጅቱ የተተገበረውን የኢንተርፕራይዝ ሐብት እቅድ(ERP) ካለሙት ባለሙያ ሙያዊ ማብራሪና ምላሽ ተሰጥቷቸዋል፡፡
በተጨማሪም በስልጠናው የተሳተፉ በቡድን ተከፍው በተዘጋጁት አራት የስልጠና ማዕከላት ውስጥ ተግባራዊ ልምምድና ሙያዊ ድጋፍ እንዲሰጣቸው ተደርጓል፡፡
ሥልጠናው በዋናነት በግዢ ጥያቄ አቀረቀረብ፣ ለሸቀጥ በሚቆረጡ ደረሰኞች አዘገጃጀት፣ በኢንቨንተሪ ማስተላለፍና ማረጋገጨዎች፣ሽያጭና ገቢን ማስታረቅ፣ የባንክ ወጪና ገቢን ማስታረቅ እና በሌሎችም ተመሳሳይ ከኢንተርፕራይዝ ሐብት እቅድ/ አስተዳደር (ERP) ጋር የተያያዙ የአሰራር ሥርዓቶች ላይ በማተኮር በተግባር የተደገፈ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡
በሥልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የኢኢግልድ ተ/የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዮናስ ዘለቀ ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ድርጅቱ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ኢ አር ፒ ተግብሮ እየሰራ ያለ እንደሆነና በዚህም ሥራ በውስጥና በውጭ ኦዲተሮች ሒሳቡ እየተረጋገጠ እንደሆነ አመልክተው በኦዲት ሪፖርቶች ላይ የሚነሱ የተለያዩ የአሰራር ችግሮችን በተለይም የአመዘጋገብና የሶፍት ዌር አጠቃቀም ክፍተቶችን መነሻ በማድረግ በተጨማሪም ድርጅቱ እየተገበረ ያለውን ነባሩን ኢ አር ፒ ሲስተም ቨርዥን በሁሉም ቅርንጫፎችና ዲስትሪክት ጽ/ቤቶች የማሳደግ ስራ ጋር በተያያዘ ስልጠናው እንደተዘጋጀ አመልክተዋል፡፡
በዚህም መሠረት የአይ ቲ እና ካሸሮችን ጨምሮ በዋና መስሪያ ቤትና ዲስትሪክት ያሉ የፋይናንስ ባለሙያዎችን በተፈጠሩ የአጠቃቀም ችግሮችና የአሰራር ስህተቶች ላይ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና እንደተሰጠ ገልጸው በስልጠናው የተካፈሉት የሽያጭ ቅርንጫፎችና የዲስትሪክት ባለሙያዎች ባለፉት ጊዜያት የታዩትን የአሰራር ስህተቶች ደግመው ሊሰሩ እንደማይገባ አጽንኦት በመስጠት ለስራቸው ትኩረት ሠጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ ማሳሰቢያና የስራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡





