ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ

Nine-month Performance Review Session Highlights Considerable Achievements
21/04/2025

EIIDE leaders and employees celebrated International Women's Day.
17/03/2025

EIIDE conducted Eight-month plan performance review
17/03/2025

Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given
11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025

Financial and Audit Report
25/10/2023

Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE
26/12/2024

Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction
02/12/2024

EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year
23/10/2024

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding
23/10/2024

A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs
14/10/2024

Congratulations !!
11/10/2024

EIIDE awarded its management and employees for the successful performance of the 2023/24 fiscal year
26/08/2024

EIIDE became the highest awardee of the Abyssinian Industrial Award
22/07/2024

Managers and employees of the Public Enterprises Holding and Administration and responsible institutions conducted sapling planting
20/07/2024

EIIDE conducted Ten-month plan implementation and 2024/25 corporate plan review of central and western districts
20/05/2024

EIIDE Reviewed it's Strategic Plan and other operating manuals
13/05/2024

EIIDE is Reviewing it's Strategic Plan and other operating manuals
10/05/2024

EIIDE participated in 'Ethiopia Tamrt' Expo
09/05/2024

EIIDE participated in the 10th International Cooperatives Exhibition and Bazaar
15/02/2024
ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ጋር በተያያዘ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ 33 የድርጅቱ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች በቢሻፍቱ ከተማ ከመጋቢት 4-8 2015 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
ለአምስት ቀናት የተሰጠው ስልጠና የድርጅቱን የአሰራር ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመጣጣኝና ዘመናዊ በማድረግ ኢኢግልድን ተወዳዳሪና ውጤታማ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አማካሪነት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራው ክትትል እንደሚከሄድም ታውቋል፡፡
ከዚህ ሥልጠና ቀደም ባሉት ጊዜያት ከጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት አንጻር በድርጅታችን ዋናው መስሪያ ቤት እና በዲስትሪክቶች በመገኘት መረጃዎችን በማሰባሰብ፣ ትንተና በማካሄድ የአሰራር ሥርዓት ክፍተት (Gap assessment) ተለይቶ የጥናት ሪፖርቱ ለማኔጅመንት የቀረበ ሲሆን ስለ ጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ገለጻ ተደርጎ በድርጅታችን ማኔጅመንቱ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በመሆኑም ለጥራት ስራ አመራር ስርዓቱ ልማትና ትግበራ የጥራት አስተባባሪ የተመደበ ሲሆን የአሰራር ስርዓቱን ለመተግበር እንዲቻል ከሁሉም የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ 33 አባላትን ያካተተ ግብረ-ኃይል ተመርጦ ወደ ስልጠናው ተገብቷል፡፡
በቀጣይም በተመሳሳይ ዘርፍ የተሰማሩ ሆነው የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ተግባራዊ ካደረጉ ድርጅቶች የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ እንዲሁም የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ትግበራ ዕውን ለማድረግ የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን፣ ፕሮሲጀር ማንዋሎችን፣ የሥራ መመሪያዎች፣ ቅጾችን እና ሌሎች ዶክመንቶችን በመለየት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ለመተግበር የሚያስፈልጉ ዶክመንቶች እንዲዘጋጁ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡
ከዚህ አንጻር በየሥራ ክፍሎች መመሪያዎች፣ ፕሮሲጀር ማንዋሎችን፣ የሥራ መመሪያዎች፣ ቅጾችን እና ሌሎች ዶክመንቶችን በመለየት በጥራት ሥራ አመራር አሠራር ሥርዓት መርህ መሠረት ተግባራዊ በማድረግ ድርጅታችን ተወዳዳሪና ውጤታማ በማድረግ፤ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን እንዲሁም የገበያ ማረጋጋት ሥራን ውጤታማ በሆነ አሰራር በመምራት ድርጅቱን ተወዳዳሪ፣ ውጤታማ እና ትርፋማ በማድረግ ለአገራችን ኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን ሚና የሚወጣ ተቋም ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡