የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ
Recognition was given to districts and branches that achieved outstanding performance in six months.
27/01/2026
Training on procurement performance guidelines and change management has been given
10/11/2025
EIIDE's first quarter performance was announced as successful.
20/10/2025
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) Receives Platinum Level Award
10/10/2025
Managers and experts of Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) participated on training held at the African Leadership Excellence Academy
25/09/2025
EIIDE Yarn Processing Center staffs conducted field visits
23/09/2025
EIIDE leaders and employees celebrated the completion of the Grand Renaissance Dam and annual workers' day
09/09/2025
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise (EIIDE) highlighted for strong performance for the 2024/25 budget year
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
Nine-month Performance Review Session Highlights Considerable Achievements
21/04/2025
EIIDE leaders and employees celebrated International Women's Day.
17/03/2025
EIIDE conducted Eight-month plan performance review
17/03/2025
Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
Financial and Audit Report
25/10/2023
Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE
26/12/2024
Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction
02/12/2024
EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year
23/10/2024
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding
23/10/2024
A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs
14/10/2024
ኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የዲስትሪክት ሃላፊዎችና ፈጻሚዎች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድን በላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የሚጠበቅባቸውን ሃለፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ፡፡
ይህ የተገለጸው የድርጅቱ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም፣ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድና በጸደቁ የድርጅቱ አራት የሥራ መመሪያዎች ላይ የማዕከላዊ፣ የምዕራብ፣ የምስራቅና ፣የሰሜንና የደቡብ ዲስትሪክቶች ሃላፊዎችና አመራሮች በተሳተፉበት ከነሐሴ 21-22 እንዲሁም ከነሐሴ 28-29ቀን 2014 ዓ.ም በሐዋሳ፣ ጅማ እና ቢሾፍቱ እና ባህር ዳር ከተሞች ባካሄዱት የምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡
በተካሄዱት የውይይት መድረኮች የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በተለይ በሐዋሳ መድረክ ላይ እንደገለጹት በውይይት መድረኩ አመራሮች እና ፈጻሚዎች በአፈጻጸም ሂደት የነበሯቸውን ሚና፣ ጥንካሬዎቻቸውንና ክፍተቶቻቸውን የገመገሙበትና ጠንካራ ጎኖቻቸውን አጠናክረው ለመቀጠል የጋራ መግባባት የተደረሰበት መድረክ እንደሆነ እንዲሁም የታዩ ክፍተቶች ታርመው በ2015 በጀት ዓመት ታላላቅ ዕቅዶችን ለማሳካት ሁሉም የድርሻውን በጋራ እና በተቀናጀ መልኩ የድርጅቱን ተልዕኮ ለማሳካት የጋራ ስምምነት የተደረሰበት መድረክ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡
በተያያዘም የድርጅቱ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ግዢና ሽያጭ ዘርፍ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ግርሻ በጅማ ከተማ በተካሄደው መድረክ የበላይ አመራሮች የዲስትሪክት ሃላፊዎችና ፈጻሚዎች በግንባር ተገናኝተው በ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2015 ዕቅድ እንዲሁም በተሻሻሉ መመሪያዎች ላይ መወያየታቸው እንደ ትልቅ የንግድ ድርጅት እየተካሄዱ ያሉትን የሪፎርም ሥራዎች በአግባቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ በተጨማሪም የ2015 በጀት ዓመት ዕቅዶችን በውጤታማነት ለመተግበር የዚህ ዓይነት መድረኮች የራሱ ሚና ያለው እንዳለው ያብራሩት አቶ ሰለሞን ቀደም ሲል ከነበረው ልማዳዊ አሠራርና አካሄድ ተወጥቶ እንደድርጅት የምንታደስበትን ጎዳና የምንይዝበት መድረክ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
በምክክር መድረኮቹ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በዝርዝር ቀርቦ ውይይት የተካሄዶበታል፡፡ በተጨማሪም በአፈጻጸም ሂደት እንቅፋት የነበሩ የስራ መመሪያዎች ከወቅቱ የድርጅቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣሙ ተደርገው የጸደቁ የስራ መመሪያዎች፤ የዲስትሪክት ሃላፊዎችና የሽያጭ ባለሙያዎች በተሳተፉባቸው መድረኮች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በመድረኮቹ የግዢ፣ የሽያጭ የፋይናንስ እና የንብረት አወጋገድ መመሪያዎች ቀርበው ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎች ተከናውኗል፡፡
በማጠቃለያም በውይይት መድረኮቹ ተሳታፊ የነበሩ የድርጅቱ የበላይና መካከለኛ አመራሮች፣ የዲስትሪክት ሃላፊዎች፣ የቡድን መሪዎች እና ባለሙያዎች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድን በላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የሚጠበቅባቸውን ሃለፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡


