ድርጅቱ ተልዕኮውን በተሟላ ሁኔታ ለማሳካትና በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪነቱን ለማጠናከር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ።
ድርጅቱ ተልዕኮውን በተሟላ ሁኔታ ለማሳካትና በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪነቱን ለማጠናከር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ።
16/03/2026
Financial and Audit Report 2023/24
25/03/2026
Financial and Audit Report 2022/23
25/03/2026
ኢኢግልድ የ2018 በጀት ዓመት 8 ወራት አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
16/03/2026
Training on ERP System had been given to employees of EIIDE
09/03/2026
Recognition was given to districts and branches that achieved outstanding performance in six months.
27/01/2026
Training on procurement performance guidelines and change management has been given
10/11/2025
EIIDE's first quarter performance was announced as successful.
20/10/2025
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) Receives Platinum Level Award
10/10/2025
Managers and experts of Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) participated on training held at the African Leadership Excellence Academy
25/09/2025
EIIDE Yarn Processing Center staffs conducted field visits
23/09/2025
EIIDE leaders and employees celebrated the completion of the Grand Renaissance Dam and annual workers' day
09/09/2025
Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise (EIIDE) highlighted for strong performance for the 2024/25 budget year
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
Nine-month Performance Review Session Highlights Considerable Achievements
21/04/2025
EIIDE leaders and employees celebrated International Women's Day.
17/03/2025
EIIDE conducted Eight-month plan performance review
17/03/2025
Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
Financial and Audit Report
25/10/2023
ይህ የተገለፀው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ) የ2018 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በገመገመበት ወቅት ነው።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ መለሰ መና እንደገለጹት፣ የተቋሙ የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግልጽ፣ ተዓማኒ እና የአመራር ቅንጅት የታየበት ነው።ተቋሙ ቀደም ሲል በከባድ ችግር ውስጥ እንደነበር ጠቅሰው፣ የአመራር ለውጥ በማድረግ ከዚያ ሁኔታ መውጣቱንና አሁን በተሻለ ሁኔታ እየሠራ መሆኑን ገልፀዋል።ተቋሙ የኦዲት ግኝቶችን በየጊዜው ማረም፣ በዓለም የሚኖረውን ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በመቋቋም ሽያጭና ትርፍን ማስቀጠል፣ አዳዲስ ደንበኞችን ማምጣት እና የገበያ ተደራሽነትን በሚዲያ መሣሪያዎች ማሳደግ እንደ ጠንካራ አፈፃፀሞች ተጠቁመዋል።
እንዲሁም በግዥና ሽያጭ ሂደቶች ጥራትን ማረጋገጥ፣ የሴቶች የአመራር ተሳትፎን ማሳደግ እና የሰው ሀብት ልማት ሥርዓቱን ማጠናከር ተቋሙን ለሌሎች ድርጅቶች አርአያ የሚያደርገው መሆኑን ገልፀዋል። በተጨማሪም የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ለመተግበር የተደረጉ ዝግጅቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል።
ድርጅቱን በቀጣይ የሀብት አስተዳደርን ማሻሻል፣ የቅርንጫፍ ቢሮዎችን ማዘመን እና የዲጂታል ስርዓት ለማስፋት የተጀመሩ ሥራዎች እንዲጠናከሩ አሳስበዋል።የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ኢንጅነር ስለሺ ኮሬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ተቋሙ ከቋሚ ኮሚቴው ጋር ይበልጥ በመተባበር ለለውጥ የሚሠራ መሆኑን ገልፀው፣ ችግሮችን በጥናት፣ በዘላቂነትና በአስተማማኝ መልኩ ከሥር መሠረቱ ለመፍታት በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ያስጠናቸው ጥናቶች ጥሩ መሆናቸውን ገልፀዋል። ይህንን ጥናት በማስተባበርና በማረጋገጥ ወደ ሥራ መግባት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በግዥ፣ በሽያጭና በተደራሽነት ዘርፎች የተቋሙ እቅዶችና አፈጻጸሞች የተሻሻሉ መሆናቸውን፣ ከኦዲት ጋር ተያይዞ የነበሩ ችግሮችም በተገቢ መንገድ መፍታታቸውን ገልፀው፤ ተቋሙን ለመለወጥ እና ሀብት ለማፍራት የሚደረጉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ይህንኑ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።ገበያውንና ወቅቱን በማየት የድርጅቱን ሕንጻ ዲዛይን በመቀየር ሙሉ በሙሉ ወደ ቢሮ አገልግሎት ለመለወጥ የተደረጉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን እና ቀሪ የግንባታ ሥራዎችን በፍጥነት ማጠናቀቅ እንደሚገባም አስረድተዋል።
በቀጣይ የድርጅቱን ይዞታ ማስከበር፣ የኢንዱስትሪ ጨው ግብዓት አቅርቦት አማራጮችን ማስፋት ትኩረት ሊደረግባቸው ይገባል ብለዋል።የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ዳዊት አዳነ በበኩላቸው፤ ድርጅቱ ብቃት ባለው የሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት፣ ጠንካራ የአቅርቦትና የግብይት ሰንሰለት በመገንባት፣ ጥራታቸውን የጠበቁ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን በማልማትና በማቅረብ እንዲሁም የተመረጡ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማድረስ፣ የሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ውጤታማነት እንዲጨምር እና የገበያ መረጋጋት እንዲፈጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት 9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙ በኢንዱስትሪ ግብዓቶች እና ውጤቶች ግዥ እና ሽያጭ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡን ጠቁመው፣ ተቋሙ በበጀት አመቱ 580 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ለቋሚ ኮሚቴው ተናግረዋል።በበጀት ዓመቱ ለኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆን ምክንያት የነበሩ ጉዳዮችን በቀጣይ በመፍታት የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ጥረት የሚደረግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡





