EIIDE laid the foundation stone for supporting educational equipment and building classrooms

11/08/2026

ለኢኢግልድ ሠራተኞች በሙሉ

21/05/2026

ለኢኢግልድ ሠራተኞች በሙሉ

21/05/2026

ድርጅቱ ተልዕኮውን በተሟላ ሁኔታ ለማሳካትና በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪነቱን ለማጠናከር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ።

16/03/2026

Financial and Audit Report 2023/24

25/03/2026

Financial and Audit Report 2022/23

25/03/2026

ኢኢግልድ የ2018 በጀት ዓመት 8 ወራት አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ

16/03/2026

Training on ERP System had been given to employees of EIIDE

09/03/2026

Recognition was given to districts and branches that achieved outstanding performance in six months.

27/01/2026

Training on procurement performance guidelines and change management has been given

10/11/2025

EIIDE's first quarter performance was announced as successful.

20/10/2025

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) Receives Platinum Level Award

10/10/2025

Managers and experts of Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise(EIIDE) participated on training held at the African Leadership Excellence Academy

25/09/2025

EIIDE Yarn Processing Center staffs conducted field visits

23/09/2025

EIIDE leaders and employees celebrated the completion of the Grand Renaissance Dam and annual workers' day

09/09/2025

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise (EIIDE) highlighted for strong performance for the 2024/25 budget year

27/08/2025

Financial and Audit Report 2021/22

12/05/2025

Nine-month Performance Review Session Highlights Considerable Achievements

21/04/2025

EIIDE leaders and employees celebrated International Women's Day.

17/03/2025

EIIDE conducted Eight-month plan performance review

17/03/2025

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 70 results.

ኢኢግልድ ከ2.7 ቢሊዮን ብር በላይ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችና ውጤቶችን አቀረበ

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ2013 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ከብር 2.7 ቢሊዮን በላይ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችና ውጤቶችን ለአምራች ኢንዱስትሪዎችና ለተጠቃሚው ህብረተሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ አቀረበ፡፡


የድርጅቱ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም እንደመለከተው ድርጅቱ ብር 322 ሚሊዮን የሚያወጡ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን ለአምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም ብር 2.4 ቢሊዮን የሚያወጡ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን ለተጠቃሚ የህብረተሰቡ ክፍሎች አሰራጭቷል፡፡


ኢኢግልድ ከኢንዱስትሪ ግብዓቶች ጋር በተያያዘ በጨርቃጨርቅና በአልባሳት፣ በቆዳ፣ በኢንዱስትሪ ጨው፣ በአግሮፕሮሰሲንግና በኮንስትራክሽን ግብዓቶች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሰርቷል፡፡ 


በዚህም መሠረት በጨርቃጨርቅ ከብር 14 ቢሊዮን በላይ፣ በቆዳ ዘርፍ ብር 526 ሺህ፣ በኢንዱስትሪ ጨው 22.44 ሚሊዮን፣ በአግሮፕሮሰሲንግ ዘርፍ ብር 48 ሚሊዮን የሚያወጡ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን ለማቅረብ ተችሏል፡፡


በተያያዘም ኢኢግልድ በመንግስት ከተሰጠው አምራች ኢንዱስትሪዎችን የመደገፍ ቁልፍ ስራ በተጨማሪ አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያመርቷቸውን የኢንዱስትሪ ውጤቶች በመረከብ በተመጣጣኝ ዋጋ ያሰራጨ ሲሆን በያዝነው በጀት ዘመት ዘጠኝ ወራት ብር 2.4 ቢሊዮን የሚያወጡ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን አቅርቧል፡፡
በኢንዱስትሪ ውጤቶች ከተቀፉት ምርቶች መካከል ብር 1.4 ቢሊዮን የምግብ ዘይት፣ ብር 891 ሚሊዮን ስኳር፣ ብር 64 ሚሊዮን የሚያወጡ የጨርቃጨርቅ ምርቶች፤ከብር 14 ሚሊዮን በላይ የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽንና ሌሎችም ምርቶች በማቅረብ በበጀት ዓመቱ የሚታየውን የመሠረታዊ ሸቀጦች ዋጋ ንረትና የምርቶች አቅርቦት ችግሮችን ለማርገብ ትኩረት ተሠጥቶ ተሰርቷል፡፡


ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ በሙሉ አቅሙ የግዢ እቅዱን ለመፈጸም እንዳይችል የተለያዩ ተግዳሮቶች ያጋጠሙት እንደሆነ ሪፖርቱ ያመለከተ ሲሆን የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት ችግር፣ ለግብዓቶች ግዢ ተደጋጋሚ ጨረታ ቢወጣም ተሳታፊ አለመኖር፣ የአቅራቢዎች የስምምነት ውል አለማክበር እና ከኢንዱስትሪ ጨው አቅራቢዎች ጋር ያለውን ችግር አለመፈታት በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡