የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ
በስድስት ወራት አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች ዕውቅና ተሰጠ
27/01/2026
በመንግሥት የልማት ድርጀቶች የግዢ አፈጻጸም መመሪያና በለውጥ ሥራዎች ላይ ሲሰጥ የነበረዉ ሥልጠና ተጠናቀቀ
10/11/2025
የኢኢግልድ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ
20/10/2025
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ሆነ
10/10/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የአመራሮች ስልጠና በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተካሔደ
25/09/2025
የኢኢግልድ የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች በፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ
23/09/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የሠራተኞችን ዓመታዊ በዓል አከበሩ
09/09/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) በበጀት ዓመቱ ጠንካራ አፈጻጸም አስመዘገበ
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
በአገራዊና ተቋማዊ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሔደ
21/04/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ
17/03/2025
የኢኢግልድ ሽያጭ ቅርንጫፎችና ዲስትሪክቶች የስምንት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
17/03/2025
በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
ማስታወቂያ
25/10/2023
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ
26/12/2024
የኢኢግልድ የበላይ አመራሮችና ሃላፊዎች በግንባታ ላይ የሚገኘውን ዋና መ/ቤት ህንፃ ጎበኙ
02/12/2024
ኢኢግልድ በበጀት ዓመቱ አራት ወራት የዕቅዱን 96 በመቶ ማከናወኑ ተገለጸ
23/10/2024
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅትና የኢትዮጵያ ፖስታ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረሙ
23/10/2024
በኢንዱስትሪ ግብዓቶች አቅርቦት ተግዳሮቶችና መፍትሄ ላይ ውይይት ተካሄደ
14/10/2024
ኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የዲስትሪክት ሃላፊዎችና ፈጻሚዎች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድን በላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የሚጠበቅባቸውን ሃለፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ፡፡
ይህ የተገለጸው የድርጅቱ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም፣ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድና በጸደቁ የድርጅቱ አራት የሥራ መመሪያዎች ላይ የማዕከላዊ፣ የምዕራብ፣ የምስራቅና ፣የሰሜንና የደቡብ ዲስትሪክቶች ሃላፊዎችና አመራሮች በተሳተፉበት ከነሐሴ 21-22 እንዲሁም ከነሐሴ 28-29ቀን 2014 ዓ.ም በሐዋሳ፣ ጅማ እና ቢሾፍቱ እና ባህር ዳር ከተሞች ባካሄዱት የምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡
በተካሄዱት የውይይት መድረኮች የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በተለይ በሐዋሳ መድረክ ላይ እንደገለጹት በውይይት መድረኩ አመራሮች እና ፈጻሚዎች በአፈጻጸም ሂደት የነበሯቸውን ሚና፣ ጥንካሬዎቻቸውንና ክፍተቶቻቸውን የገመገሙበትና ጠንካራ ጎኖቻቸውን አጠናክረው ለመቀጠል የጋራ መግባባት የተደረሰበት መድረክ እንደሆነ እንዲሁም የታዩ ክፍተቶች ታርመው በ2015 በጀት ዓመት ታላላቅ ዕቅዶችን ለማሳካት ሁሉም የድርሻውን በጋራ እና በተቀናጀ መልኩ የድርጅቱን ተልዕኮ ለማሳካት የጋራ ስምምነት የተደረሰበት መድረክ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡
በተያያዘም የድርጅቱ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ግዢና ሽያጭ ዘርፍ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ግርሻ በጅማ ከተማ በተካሄደው መድረክ የበላይ አመራሮች የዲስትሪክት ሃላፊዎችና ፈጻሚዎች በግንባር ተገናኝተው በ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2015 ዕቅድ እንዲሁም በተሻሻሉ መመሪያዎች ላይ መወያየታቸው እንደ ትልቅ የንግድ ድርጅት እየተካሄዱ ያሉትን የሪፎርም ሥራዎች በአግባቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ በተጨማሪም የ2015 በጀት ዓመት ዕቅዶችን በውጤታማነት ለመተግበር የዚህ ዓይነት መድረኮች የራሱ ሚና ያለው እንዳለው ያብራሩት አቶ ሰለሞን ቀደም ሲል ከነበረው ልማዳዊ አሠራርና አካሄድ ተወጥቶ እንደድርጅት የምንታደስበትን ጎዳና የምንይዝበት መድረክ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
በምክክር መድረኮቹ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በዝርዝር ቀርቦ ውይይት የተካሄዶበታል፡፡ በተጨማሪም በአፈጻጸም ሂደት እንቅፋት የነበሩ የስራ መመሪያዎች ከወቅቱ የድርጅቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣሙ ተደርገው የጸደቁ የስራ መመሪያዎች፤ የዲስትሪክት ሃላፊዎችና የሽያጭ ባለሙያዎች በተሳተፉባቸው መድረኮች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በመድረኮቹ የግዢ፣ የሽያጭ የፋይናንስ እና የንብረት አወጋገድ መመሪያዎች ቀርበው ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎች ተከናውኗል፡፡
በማጠቃለያም በውይይት መድረኮቹ ተሳታፊ የነበሩ የድርጅቱ የበላይና መካከለኛ አመራሮች፣ የዲስትሪክት ሃላፊዎች፣ የቡድን መሪዎች እና ባለሙያዎች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድን በላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የሚጠበቅባቸውን ሃለፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡


