በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት የሚያቀርቡ አካላት ከህገወጥ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ጥሪ ቀረበ

በአገራዊና ተቋማዊ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሔደ
21/04/2025

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ
17/03/2025

የኢኢግልድ ሽያጭ ቅርንጫፎችና ዲስትሪክቶች የስምንት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
17/03/2025

በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025

ማስታወቂያ
25/10/2023

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ
26/12/2024

የኢኢግልድ የበላይ አመራሮችና ሃላፊዎች በግንባታ ላይ የሚገኘውን ዋና መ/ቤት ህንፃ ጎበኙ
02/12/2024

ኢኢግልድ በበጀት ዓመቱ አራት ወራት የዕቅዱን 96 በመቶ ማከናወኑ ተገለጸ
23/10/2024

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅትና የኢትዮጵያ ፖስታ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረሙ
23/10/2024

በኢንዱስትሪ ግብዓቶች አቅርቦት ተግዳሮቶችና መፍትሄ ላይ ውይይት ተካሄደ
14/10/2024

እንኳን ደስ አላችሁ!!!
11/10/2024

ኢኢግልድ ላገኘው የ2016 በጀት ዓመት ስኬታማ አፈጻጸም ለአመራሮቹና ሠራተኞቹ እውቅና ሰጠ
26/08/2024

ኢኢግልድ የአቢሲኒያ ኢንዱስትሪዎች ሽልማት ከፍተኛ ተሸላሚ ሆነ
22/07/2024

የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሃላፊዎች የችግኝ ተከላ አካሄዱ
20/07/2024

የማዕከላዊና የምዕራብ ዲስትሪክት ጽ/ቤቶች አስር ወራት ዕቅድ አፈጻጸምና 2017 የኮርፖሬት ዕቅድ ግምገማ ተካሄደ
20/05/2024

ኢኢግልድ በስትራቴጂክ ዕቅዱና በአሰራር መመሪያዎች ረቂቅ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን ግምገማ አጠናቀቀ
13/05/2024

ኢኢግልድ ስትራቴጂክ ዕቅዱና ሌሎችም የአሰራር ስርዓቶቹን እየገመገመ ይገኛል
10/05/2024

ኢኢግልድ በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ ተሳተፈ
09/05/2024

ኢኢግልድ 10ኛው አገር ዓቀፍ የሕብረት ሥራ ማሕበራት ኤግዚቢሽንና ባዛር ተሳተፈ
15/02/2024
በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት በማቅረብ የህብረተሰቡን ጤና አደጋ ላይ መጣል ህገወጥ ተግባር መሆኑንና በዚህ ህገወጥ ተግባር የተሠማሩ አካላት ከዚህ ተግባራቸው እንዲታቀቡ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት እና የንግድ ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ከተማ ኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል በጥሬ ጨው አቅርቦት፣ ግብዓትና ሥርጭት ላይ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ታህሳስ 21 ቀን 2014 ዓ.ም አሳሰቡ፡፡
የኢግልድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በዚሁ መድረክ ላይ እንዳመላከቱት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ለአምራች ኢንዱስትሪዎቻችን የኢንዱስትሪ ጨው በብቸኝነት እንዲያቀርብ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተሠጠው ኃላፊነት መሠረት ወደ ሥራ ከገባ በኋላ በርካታ ችግሮችና ውጣ ውረዶችን በመጋፈጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡
አያይዘውም በኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት ሒደት ምርቱ ለማን፣ መቼ እንዴት ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚቻል የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት እያንዳንዱ የቆዳ ፋብሪካ ሰብሳቢና አቅራቢ ድርጅቶች እንዲሁም ጨው ለግብዓት የሚጠቀሙ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ምርቱን በአግባቡ በሥራ ላይ ለማዋላቸው ማረጋገጫ እንዲቀርብ የአሠራር ሥርዓት ተዘርግቶ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
ጉዳዩ በንግድና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚ/ር እና በሌሎች ተቆጣጣሪና ክትትል በሚያካሂዱ ባለድርሻ አካላት የሚጣራ ጉዳይ ሆኖ ምንጩ ከየት እንደሆነ ያልታወቀ በአዮዲን ያልበለጸገ ጨው ለህብረተሰቡ ለምግብነት ገበያ ላይ እየቀረበ እንደሚኝ የገለጹት ወ/ሮ የሺመቤት ይህ ህገወጥ ተግባር ከየትና በማን እየተከናወነ እንደሚገኝና አፋጣኝ መፍትሄ እንደሚያስፈልገውም አመልክተዋል፡፡
በተጨማሪ የኢኢግልድን ምስል በማጠልሸት የራሳቸውን የምግብ ጨው አምራች ድርጅቶቻቸውን ሀብት ለማካበትና የተሸለ ምሰል ለመገንባትና በተቃራኒው ደግሞ የኢንዱስትሪ ጨው በብቸኝነት ለአምራች ኢንዱስትሪዎችና ሌሎችም ተጓዳኝ ማህበራት የሚያቀርበውን ኢኢግልድን ከኢንዱስትሪ ጨው ንግድ ለማስወጣት የሚደረግ የሴራ አካል እንደሆነ በውይይቱ ላይ የተነሳ ሲሆን ኢኢግልድ በዚህ ዓይነት ሕገወጥ ተግባር ውስጥ ስሙ ሊነሳ እንደማይገባ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
በማጠቃለያም እየተካሔደ ያለው በአዮዲን ያልበለጸገ የምግብ ጨው ሥርጭት የህብረተሰቡን ጤና በእጅጉ የሚጐዳ በመሆኑ በዚህ ተግባር የተሠማሩ ሕገወጥ አካላትን በሚመለከታቸው ተቆጣጣሪ የመንግሥት ተቋማት ክትትል በማድረግ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝና በቀጣይም ክትትሉ፣ ቁጥጥሩና የሚወሰደውም ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በምክክር መድረኩ ላይ ተሳታፊ የነበሩ የንግድና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር፣ የሚመለከታቸው ባለድርሻና ተቆጣጣሪ መ/ቤቶች ኃላፊዎች አጽንኦት በመስጠት አሳስበዋል፡፡
በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ በኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት፣ ስርጭትና ግብይት ዙሪያ አቶ ዮናታን ሲሳይ በኢኢግልድ የግብዓት ግዢና ሽያጭ ዘርፍ የቃሊቲ ዲስትሪክት ሃላፊ አጭር ጥናታዊ ጽሁፍ ለተካሄደው ውይይት በመነሻነት አቅርበዋል፡፡
በውይይት መድረኩ በቆዳ ዘርፍ የተሰማሩ አምራቾች፣ የቆዳ ኢንስቲትዩት፣ የንግድ ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የምግብና መድሃኒት አስተዳደር ባለሥልጣንና ሌሎችም ጉዳዩ በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡