ኢኢግልድ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ሰጠ::
በስድስት ወራት አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች ዕውቅና ተሰጠ
27/01/2026
በመንግሥት የልማት ድርጀቶች የግዢ አፈጻጸም መመሪያና በለውጥ ሥራዎች ላይ ሲሰጥ የነበረዉ ሥልጠና ተጠናቀቀ
10/11/2025
የኢኢግልድ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ
20/10/2025
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ሆነ
10/10/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የአመራሮች ስልጠና በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተካሔደ
25/09/2025
የኢኢግልድ የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች በፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ
23/09/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የሠራተኞችን ዓመታዊ በዓል አከበሩ
09/09/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) በበጀት ዓመቱ ጠንካራ አፈጻጸም አስመዘገበ
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
በአገራዊና ተቋማዊ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሔደ
21/04/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ
17/03/2025
የኢኢግልድ ሽያጭ ቅርንጫፎችና ዲስትሪክቶች የስምንት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
17/03/2025
በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
ማስታወቂያ
25/10/2023
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ
26/12/2024
የኢኢግልድ የበላይ አመራሮችና ሃላፊዎች በግንባታ ላይ የሚገኘውን ዋና መ/ቤት ህንፃ ጎበኙ
02/12/2024
ኢኢግልድ በበጀት ዓመቱ አራት ወራት የዕቅዱን 96 በመቶ ማከናወኑ ተገለጸ
23/10/2024
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅትና የኢትዮጵያ ፖስታ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረሙ
23/10/2024
በኢንዱስትሪ ግብዓቶች አቅርቦት ተግዳሮቶችና መፍትሄ ላይ ውይይት ተካሄደ
14/10/2024
ኢኢግልድ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ሰጠ
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢኢግልድ) እየተካሄደ ያለውን የሀገር ህልውናን የማዳን ዘመቻ መነሻ በማድረግ ሀገር ለመከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ እና ድርጅቱ በ2013 በጀት ዓመት ያስመዘገበውን አጥጋቢ ውጤት ምክንያት በማድረግ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የድርጅቱ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ነሐሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም ሰጠ፡፡
ለሠራዊታችን ድጋፉ የተሰጠው ኢኢግልድ በ2013 በጀት ዓመት ያስመዘገበውን የላቀ አፈጻጸም ምክንያት በማድረግ በድርጅቱ ቅጥር ጊቢ አጥጋቢ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች ዕውቅናና ሽልማት ለመስጠት ባዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ ሲሆን በሥነሥርዓቱም ላይ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ክብርት ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ተወካይ አስረክበዋል፡፡
በድጋፍ አሰጣጡ ስነስርዓት ላይ ከሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የመከላከያ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ ብ/ጄነራል አስረስ አያሌው እእንደገለጹት ከሀገራችን የቅርብ፣ የሩቅ የውስጥ ጠላቶች ጋር በማበር ሀገር ለማፈራረስ እየሰራ የሚገኘው ፀረ-ህዝብ ቡድን ለማስወገድ ሠራዊቱ ቀን ከሌሊት እየተዋደቀ የሚገኝ ሲሆን በተለይ ይህ ህገ ወጥ ቡድን በአማራና አፋር በአጎራባች ስፍራዎች ጥቃቱን ለማስፋፋት የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ለመግታት በሰራዊቱ የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኖች ከሠጡት የቁሳቁስ ድጋፍ በተጨማሪ አሁን በገንዘብ ተደረገው የ2 ሚሊየን ብር ድጋፍና በድርጅቱ ከሚሰሩ ሠራተኞች መካከል በፈቃደኝነት ለመዝመት መነሳሳታቸው ለሰራዊቱ ተጨማሪ ስንቅ እንደሚሆነው ሃላፊው አመልክተዋል፡፡
በተያያዘም በዋናነት ድርጅቱ የ2013 በጀት ዓመት ያስመዘገበውን የላቀ ውጤት መነሻ በማድረግ ባካሄደው የእውቅናና የሽልማት መርሃግብር የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መላኩ አለበል፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታና የኢኢግልድ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ተካ ገ/የስ እንዲሁም የተከበሩ ወ/ሮ መሠረት አባተ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ኢንዱስትሪ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የኢኢግልድ የስራ አመራር ቦርድ አባላት ተገኝተዋል፡፡
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በዕውቅናና ሽልማት ስነስርት ላይ አገራችን በሪፎርም ውስጥ እንደምትገኝ አመልክተው በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ፣ በመከላከያ እና በሌሎችም ዘርፎች እተካሄደ ያለው ሪፎርም ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነና በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ውስጥ እየተካሄደ ያለው የሪፎርም ሥራ በተለይም በአመራር፣ በአሰራር፣ በቴክኖሎጂ እና በዲጂታል አውቶሜሽን ስራዎች የሚያበረታቱና ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ ላስመዘገበው ውጤት አስዋጽኦ እንዳላቸው አመልክተዋል፡፡
ኢኢግልድ ባለፉት ዓመታት የነበሩበትን የተወሳሰቡ ችግሮች በአብዛኛው እንደተወጣና በተካሄዱትም የለውጥ ስራዎች ድርጅቱን ከውድቀት በመታደግ በ2013 በጀት ዓመት የተገኘው ውጤት የሚያበረታታና በቀጣዩም ዓመት የተሸለ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ከፍተኛ ርብርብ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡
የኢኢግልድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ክብርት ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በስነ ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ድርጅቱ ባለፉት ዓመታት ካለፈባቸው የተወሳሰቡ የአሰራር፣ የአደረጃጀት፣ የግብዓት፣ የብልሹ አሰራር፣የቡድንተኝነት፣ የአሰራር እና አሳተፊነት ችግሮች ተወጥቶ አሁን የሚገኝበት ደረጃ ለመድረስ እልህ አስጨራሽ ችግሮች እንዳጋጠሟቸው በዝርዝር አመልክተው የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የድርጅቱ የስራ አመራር ቦርድ እና የድርጅቱ አመራሮች ስትራቴጂክ ውሳኔዎችን በመወሰን በአሁኑ ወቅት ችግሩን ተወጥተው በ2013 በጀት ዓመት በድርጅቱ ታሪክ ተገኝቶ የማይታወቀውን 96.7 በመቶ እቅድ አፈጻጸም እንደተመዘገበ አመልክተዋል፡፡
በመጨረሻም በዚህ ዓመት የተገኘውን ውጤት ምክንያት በማድረግ ይህንን ውጤት ላስመዘገቡና ለተገኘውም ውጤት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የበላይ ሃላፊዎች፣የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች፣ እጅግ ባነሰ ደሞዝ ድርጅቱን ድርጅቴ ብለው 25 እና ከዚያ በላይ ላገለገሉ ሠራተኞች እንዲሁም በክብር በጡረታ ለተገለሉ ሠራተኞች ይህ የእውቅና መርሃግብር እንደተዘጋጀ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በአገራችን የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ያለባቸውን የግብዓት አቅርቦት ችግር ለመፍታት በዋናነት በኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት ስራ ላይ ተሰማራ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡
