Financial and Audit Report 2023/24

25/03/2026

Financial and Audit Report 2022/23

25/03/2026

ኢኢግልድ የ2018 በጀት ዓመት 8 ወራት አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ

16/03/2026

ሙያን መሠረት አድርጎ የሚሰጥ ተከታታይ ስልጠና ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ

09/03/2026

በስድስት ወራት አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች ዕውቅና ተሰጠ

27/01/2026

በመንግሥት የልማት ድርጀቶች የግዢ አፈጻጸም መመሪያና በለውጥ ሥራዎች ላይ ሲሰጥ የነበረዉ ሥልጠና ተጠናቀቀ

10/11/2025

የኢኢግልድ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ

20/10/2025

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ሆነ

10/10/2025

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የአመራሮች ስልጠና በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተካሔደ

25/09/2025

የኢኢግልድ የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች በፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ

23/09/2025

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የሠራተኞችን ዓመታዊ በዓል አከበሩ

09/09/2025

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) በበጀት ዓመቱ ጠንካራ አፈጻጸም አስመዘገበ

27/08/2025

Financial and Audit Report 2021/22

12/05/2025

በአገራዊና ተቋማዊ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሔደ

21/04/2025

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ

17/03/2025

የኢኢግልድ ሽያጭ ቅርንጫፎችና ዲስትሪክቶች የስምንት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ

17/03/2025

በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21

28/01/2025

ማስታወቂያ

25/10/2023

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ

26/12/2024

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 66 results.

ኢኢግልድ የዲስትሪክቶችን የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ግምገማ አካሄደ

 

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢግልድ) የዲስትሪክቶች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም የተለያዩ ውስጣዊና ውጪያዊ ተግዳሮቶች ቢያጋጥሙትም ጥሩ ውጤትና የሚያበረታታ አፈጻጸም የተመዘገበበት መሆኑን የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ ገለጹ፡፡

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይህንን የገለጹት የድርጅቱ የበጀት ዓመት አፈጻጸምና ዕቅድ እንዲሁም የዲስትሪክቶች የበጀት ዓመቱ አፈጻጸምና ዕቅድ ግምገማና ውይይት ከነሐሴ 13-14/2015 ዓ.ም በግዮን ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡

አያይዘውም የድርጅቱ አፈጻጸም አበረታች ቢሆንም በአፈጻጸም ወቅት የታዩ ክፍተቶች ተለይተው በቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የሚታረሙበት የአሰራር ሥርዓት ተዘርግተውላቸው አጥጋቢ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡

በዚሁ መድረክ የማዕከላዊ፣ የምስራቅ፣ የምዕራብና የደቡብ ዲስትሪክቶች ሥር የሚገኙ የሽያጭ ቅርንጫፎች ዕቅድ አፈጻጸምና የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ በዲስትሪክቶቹ ሃላፊዎች እንዲሁም የድርጅቱ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2016 ዕቅድ በስትራቴጂክ ሥራ አመራር ዳይሬክተር ቀርቦ ግምገማና ውይይት ተካሂዶ የጋራ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ ተሰርቷል፡፡

በሁለቱ ቀናት  ውይይት ዲስትሪክቶች ከዕቅድ እስከ አፈጻጸም ተናበው ለመስራት ያደረጓቸው ጥረቶችና የተገኙ ውጤቶች(የታዩ ክፍተቶች እንዳሉ ሆነው)አበረታች መሆናቸው፣ ሁሉም ዲስትሪክቶች ዕቅዶቻቸውን ከኮርፖሬት ዕቅዱ ጋር በመናበብ ለመፈጸም ያደረጉት ጥረት ሊበረታታ የሚገባው እንደሆነ፣ በሽያጭ ቅርንጫፎቻችን የሚገኙ የሸቀጦች ክምችት ጋር በተያያዘ ነባሩ አሠራር ትኩረት ሊሰጠውና ሊሻሻል እንደሚገባ፣ ለደንበኞች የተሠጠው ትኩረት ካለፉት ዓመታት የተሻለ ቢሆንም አሁንም ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት እንዳለበትና ሌሎችም ዓበይት ጉዳዮች ተነስተው የጋራ ግንዛቤ የተጨበጠባቸው ሲሆን ለግብዓት ግዢ የተገኘውን ብድር በጥቅም ላይ ማዋል፣ የድርጅቱ የሒሳብ ምርመራ፣ እየተገበሩ የሚገኙ ፕሮጀክቶች እና የሪፎርም ሥራዎች ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች እንደሆኑ ተብራርቷል፡፡

በሁለቱ ቀናት በአዳራሽ ከተካሄደው የውይይት በተጨማሪ የበላይ አመራሮች፣ የዲስትሪክት ሃላፊዎችና ባለሙያዎች በግንባታ ላይ የሚገኘውን ባለ 18 ወለል የዋና መ/ቤት ሕንፃ ፕሮጀክት እንዲጎበኙና በፕሮጀክቱ የሚገኝበትን ደረጃ እንዲረዱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ማብራሪያ  በፕሮጀከቱ ሃላፊ  ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡