ኢኢግልድ የዲስትሪክቶችን የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ግምገማ አካሄደ
Financial and Audit Report 2023/24
25/03/2026
Financial and Audit Report 2022/23
25/03/2026
ኢኢግልድ የ2018 በጀት ዓመት 8 ወራት አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
16/03/2026
ሙያን መሠረት አድርጎ የሚሰጥ ተከታታይ ስልጠና ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ
09/03/2026
በስድስት ወራት አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች ዕውቅና ተሰጠ
27/01/2026
በመንግሥት የልማት ድርጀቶች የግዢ አፈጻጸም መመሪያና በለውጥ ሥራዎች ላይ ሲሰጥ የነበረዉ ሥልጠና ተጠናቀቀ
10/11/2025
የኢኢግልድ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ
20/10/2025
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ሆነ
10/10/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የአመራሮች ስልጠና በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተካሔደ
25/09/2025
የኢኢግልድ የክር ማጠንጠኞ ማዕከል ሰራተኞች በፋብሪካዎች ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ
23/09/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የሠራተኞችን ዓመታዊ በዓል አከበሩ
09/09/2025
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) በበጀት ዓመቱ ጠንካራ አፈጻጸም አስመዘገበ
27/08/2025
Financial and Audit Report 2021/22
12/05/2025
በአገራዊና ተቋማዊ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሔደ
21/04/2025
የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ
17/03/2025
የኢኢግልድ ሽያጭ ቅርንጫፎችና ዲስትሪክቶች የስምንት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
17/03/2025
በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
11/03/2025
Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025
ማስታወቂያ
25/10/2023
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ
26/12/2024
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢግልድ) የዲስትሪክቶች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም የተለያዩ ውስጣዊና ውጪያዊ ተግዳሮቶች ቢያጋጥሙትም ጥሩ ውጤትና የሚያበረታታ አፈጻጸም የተመዘገበበት መሆኑን የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ ገለጹ፡፡
የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይህንን የገለጹት የድርጅቱ የበጀት ዓመት አፈጻጸምና ዕቅድ እንዲሁም የዲስትሪክቶች የበጀት ዓመቱ አፈጻጸምና ዕቅድ ግምገማና ውይይት ከነሐሴ 13-14/2015 ዓ.ም በግዮን ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡
አያይዘውም የድርጅቱ አፈጻጸም አበረታች ቢሆንም በአፈጻጸም ወቅት የታዩ ክፍተቶች ተለይተው በቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የሚታረሙበት የአሰራር ሥርዓት ተዘርግተውላቸው አጥጋቢ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡
በዚሁ መድረክ የማዕከላዊ፣ የምስራቅ፣ የምዕራብና የደቡብ ዲስትሪክቶች ሥር የሚገኙ የሽያጭ ቅርንጫፎች ዕቅድ አፈጻጸምና የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ በዲስትሪክቶቹ ሃላፊዎች እንዲሁም የድርጅቱ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2016 ዕቅድ በስትራቴጂክ ሥራ አመራር ዳይሬክተር ቀርቦ ግምገማና ውይይት ተካሂዶ የጋራ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ ተሰርቷል፡፡
በሁለቱ ቀናት ውይይት ዲስትሪክቶች ከዕቅድ እስከ አፈጻጸም ተናበው ለመስራት ያደረጓቸው ጥረቶችና የተገኙ ውጤቶች(የታዩ ክፍተቶች እንዳሉ ሆነው)አበረታች መሆናቸው፣ ሁሉም ዲስትሪክቶች ዕቅዶቻቸውን ከኮርፖሬት ዕቅዱ ጋር በመናበብ ለመፈጸም ያደረጉት ጥረት ሊበረታታ የሚገባው እንደሆነ፣ በሽያጭ ቅርንጫፎቻችን የሚገኙ የሸቀጦች ክምችት ጋር በተያያዘ ነባሩ አሠራር ትኩረት ሊሰጠውና ሊሻሻል እንደሚገባ፣ ለደንበኞች የተሠጠው ትኩረት ካለፉት ዓመታት የተሻለ ቢሆንም አሁንም ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት እንዳለበትና ሌሎችም ዓበይት ጉዳዮች ተነስተው የጋራ ግንዛቤ የተጨበጠባቸው ሲሆን ለግብዓት ግዢ የተገኘውን ብድር በጥቅም ላይ ማዋል፣ የድርጅቱ የሒሳብ ምርመራ፣ እየተገበሩ የሚገኙ ፕሮጀክቶች እና የሪፎርም ሥራዎች ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች እንደሆኑ ተብራርቷል፡፡
በሁለቱ ቀናት በአዳራሽ ከተካሄደው የውይይት በተጨማሪ የበላይ አመራሮች፣ የዲስትሪክት ሃላፊዎችና ባለሙያዎች በግንባታ ላይ የሚገኘውን ባለ 18 ወለል የዋና መ/ቤት ሕንፃ ፕሮጀክት እንዲጎበኙና በፕሮጀክቱ የሚገኝበትን ደረጃ እንዲረዱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ማብራሪያ በፕሮጀከቱ ሃላፊ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡



