Nine-month Performance Review Session Highlights Considerable Achievements

21/04/2025

EIIDE leaders and employees celebrated International Women's Day.

17/03/2025

EIIDE conducted Eight-month plan performance review

17/03/2025

Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given

11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21

28/01/2025

Financial and Audit Report

25/10/2023

Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE

26/12/2024

Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction

02/12/2024

EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year

23/10/2024

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding

23/10/2024

A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs

14/10/2024

Congratulations !!

11/10/2024

EIIDE awarded its management and employees for the successful performance of the 2023/24 fiscal year

26/08/2024

EIIDE became the highest awardee of the Abyssinian Industrial Award

22/07/2024

Managers and employees of the Public Enterprises Holding and Administration and responsible institutions conducted sapling planting

20/07/2024

EIIDE conducted Ten-month plan implementation and 2024/25 corporate plan review of central and western districts

20/05/2024

EIIDE Reviewed it's Strategic Plan and other operating manuals

13/05/2024

EIIDE is Reviewing it's Strategic Plan and other operating manuals

10/05/2024

EIIDE participated in 'Ethiopia Tamrt' Expo

09/05/2024

EIIDE participated in the 10th International Cooperatives Exhibition and Bazaar

15/02/2024

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 53 results.

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት የሚያቀርቡ አካላት ከህገወጥ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ጥሪ ቀረበ

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት በማቅረብ የህብረተሰቡን ጤና አደጋ ላይ መጣል ህገወጥ ተግባር መሆኑንና በዚህ ህገወጥ ተግባር የተሠማሩ አካላት ከዚህ ተግባራቸው እንዲታቀቡ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት እና የንግድ ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ከተማ ኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል በጥሬ ጨው አቅርቦት፣ ግብዓትና ሥርጭት ላይ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ታህሳስ 21 ቀን 2014 ዓ.ም አሳሰቡ፡፡

የኢግልድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በዚሁ መድረክ ላይ እንዳመላከቱት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ለአምራች ኢንዱስትሪዎቻችን የኢንዱስትሪ ጨው በብቸኝነት እንዲያቀርብ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተሠጠው ኃላፊነት መሠረት ወደ ሥራ ከገባ በኋላ በርካታ ችግሮችና ውጣ ውረዶችን በመጋፈጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡

አያይዘውም በኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት ሒደት ምርቱ ለማን፣ መቼ እንዴት ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚቻል የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት እያንዳንዱ የቆዳ ፋብሪካ ሰብሳቢና አቅራቢ ድርጅቶች እንዲሁም ጨው ለግብዓት የሚጠቀሙ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ምርቱን በአግባቡ በሥራ ላይ ለማዋላቸው ማረጋገጫ እንዲቀርብ የአሠራር ሥርዓት ተዘርግቶ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ጉዳዩ በንግድና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚ/ር እና በሌሎች ተቆጣጣሪና ክትትል በሚያካሂዱ ባለድርሻ አካላት የሚጣራ ጉዳይ ሆኖ ምንጩ ከየት እንደሆነ ያልታወቀ በአዮዲን ያልበለጸገ ጨው ለህብረተሰቡ ለምግብነት ገበያ ላይ እየቀረበ እንደሚኝ የገለጹት ወ/ሮ የሺመቤት ይህ ህገወጥ ተግባር ከየትና በማን እየተከናወነ እንደሚገኝና አፋጣኝ መፍትሄ እንደሚያስፈልገውም አመልክተዋል፡፡

በተጨማሪ የኢኢግልድን ምስል በማጠልሸት የራሳቸውን የምግብ ጨው አምራች ድርጅቶቻቸውን ሀብት ለማካበትና የተሸለ ምሰል ለመገንባትና በተቃራኒው ደግሞ የኢንዱስትሪ ጨው በብቸኝነት ለአምራች ኢንዱስትሪዎችና ሌሎችም ተጓዳኝ ማህበራት የሚያቀርበውን ኢኢግልድን ከኢንዱስትሪ ጨው ንግድ ለማስወጣት የሚደረግ የሴራ አካል እንደሆነ በውይይቱ ላይ የተነሳ ሲሆን ኢኢግልድ በዚህ ዓይነት ሕገወጥ ተግባር ውስጥ ስሙ ሊነሳ እንደማይገባ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡

በማጠቃለያም እየተካሔደ ያለው በአዮዲን ያልበለጸገ የምግብ ጨው ሥርጭት የህብረተሰቡን ጤና በእጅጉ የሚጐዳ በመሆኑ በዚህ ተግባር የተሠማሩ ሕገወጥ አካላትን በሚመለከታቸው ተቆጣጣሪ የመንግሥት ተቋማት ክትትል በማድረግ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝና በቀጣይም ክትትሉ፣ ቁጥጥሩና የሚወሰደውም ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በምክክር መድረኩ ላይ ተሳታፊ የነበሩ የንግድና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር፣ የሚመለከታቸው ባለድርሻና ተቆጣጣሪ መ/ቤቶች ኃላፊዎች አጽንኦት በመስጠት አሳስበዋል፡፡

በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ በኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት፣ ስርጭትና ግብይት ዙሪያ አቶ ዮናታን ሲሳይ በኢኢግልድ የግብዓት ግዢና ሽያጭ ዘርፍ የቃሊቲ ዲስትሪክት ሃላፊ አጭር ጥናታዊ ጽሁፍ ለተካሄደው ውይይት በመነሻነት አቅርበዋል፡፡

በውይይት መድረኩ በቆዳ ዘርፍ የተሰማሩ አምራቾች፣ የቆዳ ኢንስቲትዩት፣ የንግድ ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የምግብና መድሃኒት አስተዳደር ባለሥልጣንና ሌሎችም ጉዳዩ በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡