Members of the Standing Committee on Trade and Industry of the House of peoples Representatives visited EIIDE

29/01/2024

EIIDE conducted Six month Plan performance Evaluation

17/01/2024

Sales Announcement

27/11/2023

Announcement regarding the supply of premix needed to enrich cooking oil with vitamins

06/11/2023

EIIDE evaluates its first quarter plan performance at Elilly Hotel

06/11/2023

Notice

25/10/2023

EIIDE donated 4.2 million birr sanitary pad

17/10/2023

EIIDE offered 16.5 million liters of edible oil at a reasonable price

14/09/2023

EIIDE conducted an evaluation of the of the 2022/23 fiscal year plan and the next year's plan of the enterprise

23/08/2023

Members of the Management Board visited projects of EIIDE

31/07/2023

Managers and Employees of EIIDE Conducted Green Legacy

27/07/2023

EIIDE has launched a women's workers forum

20/07/2023

ኢኢግልድ የ2015 በጀት ዓመት የስምንት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ

11/04/2023

ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ

23/03/2023

ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ

18/01/2023

አርአያነት ያለው ተግባር

14/09/2022

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፍጆታ ምርቶች መሸጫ ዋጋ

09/09/2022

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ

29/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ

07/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ9ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ ምርትና አገልግሎቱን አስተዋወቀ

09/02/2022

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 34 results.

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት የሚያቀርቡ አካላት ከህገወጥ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ጥሪ ቀረበ

በአዮዲን ያልበለጸገ ጥሬ ጨው ለምግብነት በማቅረብ የህብረተሰቡን ጤና አደጋ ላይ መጣል ህገወጥ ተግባር መሆኑንና በዚህ ህገወጥ ተግባር የተሠማሩ አካላት ከዚህ ተግባራቸው እንዲታቀቡ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት እና የንግድ ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ከተማ ኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል በጥሬ ጨው አቅርቦት፣ ግብዓትና ሥርጭት ላይ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ታህሳስ 21 ቀን 2014 ዓ.ም አሳሰቡ፡፡

የኢግልድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በዚሁ መድረክ ላይ እንዳመላከቱት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ለአምራች ኢንዱስትሪዎቻችን የኢንዱስትሪ ጨው በብቸኝነት እንዲያቀርብ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተሠጠው ኃላፊነት መሠረት ወደ ሥራ ከገባ በኋላ በርካታ ችግሮችና ውጣ ውረዶችን በመጋፈጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡

አያይዘውም በኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት ሒደት ምርቱ ለማን፣ መቼ እንዴት ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚቻል የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት እያንዳንዱ የቆዳ ፋብሪካ ሰብሳቢና አቅራቢ ድርጅቶች እንዲሁም ጨው ለግብዓት የሚጠቀሙ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ምርቱን በአግባቡ በሥራ ላይ ለማዋላቸው ማረጋገጫ እንዲቀርብ የአሠራር ሥርዓት ተዘርግቶ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ጉዳዩ በንግድና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚ/ር እና በሌሎች ተቆጣጣሪና ክትትል በሚያካሂዱ ባለድርሻ አካላት የሚጣራ ጉዳይ ሆኖ ምንጩ ከየት እንደሆነ ያልታወቀ በአዮዲን ያልበለጸገ ጨው ለህብረተሰቡ ለምግብነት ገበያ ላይ እየቀረበ እንደሚኝ የገለጹት ወ/ሮ የሺመቤት ይህ ህገወጥ ተግባር ከየትና በማን እየተከናወነ እንደሚገኝና አፋጣኝ መፍትሄ እንደሚያስፈልገውም አመልክተዋል፡፡

በተጨማሪ የኢኢግልድን ምስል በማጠልሸት የራሳቸውን የምግብ ጨው አምራች ድርጅቶቻቸውን ሀብት ለማካበትና የተሸለ ምሰል ለመገንባትና በተቃራኒው ደግሞ የኢንዱስትሪ ጨው በብቸኝነት ለአምራች ኢንዱስትሪዎችና ሌሎችም ተጓዳኝ ማህበራት የሚያቀርበውን ኢኢግልድን ከኢንዱስትሪ ጨው ንግድ ለማስወጣት የሚደረግ የሴራ አካል እንደሆነ በውይይቱ ላይ የተነሳ ሲሆን ኢኢግልድ በዚህ ዓይነት ሕገወጥ ተግባር ውስጥ ስሙ ሊነሳ እንደማይገባ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡

በማጠቃለያም እየተካሔደ ያለው በአዮዲን ያልበለጸገ የምግብ ጨው ሥርጭት የህብረተሰቡን ጤና በእጅጉ የሚጐዳ በመሆኑ በዚህ ተግባር የተሠማሩ ሕገወጥ አካላትን በሚመለከታቸው ተቆጣጣሪ የመንግሥት ተቋማት ክትትል በማድረግ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝና በቀጣይም ክትትሉ፣ ቁጥጥሩና የሚወሰደውም ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በምክክር መድረኩ ላይ ተሳታፊ የነበሩ የንግድና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር፣ የሚመለከታቸው ባለድርሻና ተቆጣጣሪ መ/ቤቶች ኃላፊዎች አጽንኦት በመስጠት አሳስበዋል፡፡

በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ በኢንዱስትሪ ጨው አቅርቦት፣ ስርጭትና ግብይት ዙሪያ አቶ ዮናታን ሲሳይ በኢኢግልድ የግብዓት ግዢና ሽያጭ ዘርፍ የቃሊቲ ዲስትሪክት ሃላፊ አጭር ጥናታዊ ጽሁፍ ለተካሄደው ውይይት በመነሻነት አቅርበዋል፡፡

በውይይት መድረኩ በቆዳ ዘርፍ የተሰማሩ አምራቾች፣ የቆዳ ኢንስቲትዩት፣ የንግድ ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የምግብና መድሃኒት አስተዳደር ባለሥልጣንና ሌሎችም ጉዳዩ በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡