Members of the Standing Committee on Trade and Industry of the House of peoples Representatives visited EIIDE

29/01/2024

EIIDE conducted Six month Plan performance Evaluation

17/01/2024

Sales Announcement

27/11/2023

Announcement regarding the supply of premix needed to enrich cooking oil with vitamins

06/11/2023

EIIDE evaluates its first quarter plan performance at Elilly Hotel

06/11/2023

Notice

25/10/2023

EIIDE donated 4.2 million birr sanitary pad

17/10/2023

EIIDE offered 16.5 million liters of edible oil at a reasonable price

14/09/2023

EIIDE conducted an evaluation of the of the 2022/23 fiscal year plan and the next year's plan of the enterprise

23/08/2023

Members of the Management Board visited projects of EIIDE

31/07/2023

Managers and Employees of EIIDE Conducted Green Legacy

27/07/2023

EIIDE has launched a women's workers forum

20/07/2023

ኢኢግልድ የ2015 በጀት ዓመት የስምንት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ

11/04/2023

ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ

23/03/2023

ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ

18/01/2023

አርአያነት ያለው ተግባር

14/09/2022

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የፍጆታ ምርቶች መሸጫ ዋጋ

09/09/2022

የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ

29/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አመራሮችና ሠራተኞች ለአቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት የማስጀመር እና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናወኑ

07/08/2022

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ9ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ ምርትና አገልግሎቱን አስተዋወቀ

09/02/2022

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 34 results.

ኢኢግልድ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ሰጠ::

ኢኢግልድ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ሰጠ

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢኢግልድ) እየተካሄደ ያለውን የሀገር ህልውናን የማዳን ዘመቻ መነሻ በማድረግ ሀገር ለመከላከያ ሠራዊት የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ እና ድርጅቱ በ2013 በጀት ዓመት ያስመዘገበውን አጥጋቢ ውጤት ምክንያት በማድረግ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የድርጅቱ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅናና ሽልማት ነሐሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም ሰጠ፡፡

ለሠራዊታችን ድጋፉ የተሰጠው ኢኢግልድ በ2013 በጀት ዓመት ያስመዘገበውን የላቀ አፈጻጸም ምክንያት በማድረግ በድርጅቱ ቅጥር ጊቢ አጥጋቢ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮችና ሠራተኞች ዕውቅናና ሽልማት ለመስጠት ባዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ ሲሆን በሥነሥርዓቱም ላይ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ክብርት ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ተወካይ አስረክበዋል፡፡

በድጋፍ አሰጣጡ ስነስርዓት ላይ ከሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የመከላከያ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ ብ/ጄነራል አስረስ አያሌው እእንደገለጹት ከሀገራችን የቅርብ፣ የሩቅ የውስጥ ጠላቶች ጋር በማበር ሀገር ለማፈራረስ እየሰራ የሚገኘው ፀረ-ህዝብ ቡድን ለማስወገድ ሠራዊቱ ቀን ከሌሊት እየተዋደቀ የሚገኝ ሲሆን በተለይ ይህ ህገ ወጥ ቡድን በአማራና አፋር በአጎራባች ስፍራዎች ጥቃቱን ለማስፋፋት የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ለመግታት በሰራዊቱ የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኖች ከሠጡት የቁሳቁስ ድጋፍ በተጨማሪ አሁን በገንዘብ ተደረገው የ2 ሚሊየን ብር ድጋፍና በድርጅቱ ከሚሰሩ ሠራተኞች መካከል በፈቃደኝነት ለመዝመት መነሳሳታቸው ለሰራዊቱ ተጨማሪ ስንቅ እንደሚሆነው ሃላፊው አመልክተዋል፡፡

በተያያዘም በዋናነት ድርጅቱ የ2013 በጀት ዓመት ያስመዘገበውን የላቀ ውጤት መነሻ በማድረግ ባካሄደው የእውቅናና የሽልማት መርሃግብር የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መላኩ አለበል፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታና የኢኢግልድ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ተካ ገ/የስ እንዲሁም የተከበሩ ወ/ሮ መሠረት አባተ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ኢንዱስትሪ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የኢኢግልድ የስራ አመራር ቦርድ አባላት ተገኝተዋል፡፡

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በዕውቅናና ሽልማት ስነስርት ላይ አገራችን በሪፎርም ውስጥ እንደምትገኝ አመልክተው በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ፣ በመከላከያ እና በሌሎችም ዘርፎች እተካሄደ ያለው ሪፎርም ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነና በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ውስጥ እየተካሄደ ያለው የሪፎርም ሥራ በተለይም በአመራር፣ በአሰራር፣ በቴክኖሎጂ እና በዲጂታል አውቶሜሽን ስራዎች የሚያበረታቱና ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ ላስመዘገበው ውጤት አስዋጽኦ እንዳላቸው አመልክተዋል፡፡

ኢኢግልድ ባለፉት ዓመታት የነበሩበትን የተወሳሰቡ ችግሮች በአብዛኛው እንደተወጣና በተካሄዱትም የለውጥ ስራዎች ድርጅቱን ከውድቀት በመታደግ በ2013 በጀት ዓመት የተገኘው ውጤት የሚያበረታታና በቀጣዩም ዓመት የተሸለ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ከፍተኛ ርብርብ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡

የኢኢግልድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ክብርት ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ በስነ ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ድርጅቱ ባለፉት ዓመታት ካለፈባቸው የተወሳሰቡ የአሰራር፣ የአደረጃጀት፣ የግብዓት፣ የብልሹ አሰራር፣የቡድንተኝነት፣ የአሰራር እና አሳተፊነት ችግሮች ተወጥቶ አሁን የሚገኝበት ደረጃ ለመድረስ እልህ አስጨራሽ ችግሮች እንዳጋጠሟቸው በዝርዝር አመልክተው የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የድርጅቱ የስራ አመራር ቦርድ እና የድርጅቱ አመራሮች ስትራቴጂክ ውሳኔዎችን በመወሰን በአሁኑ ወቅት ችግሩን ተወጥተው በ2013 በጀት ዓመት በድርጅቱ ታሪክ ተገኝቶ የማይታወቀውን 96.7 በመቶ እቅድ አፈጻጸም እንደተመዘገበ አመልክተዋል፡፡

በመጨረሻም በዚህ ዓመት የተገኘውን ውጤት ምክንያት በማድረግ ይህንን ውጤት ላስመዘገቡና ለተገኘውም ውጤት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የበላይ ሃላፊዎች፣የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣የኢኢግልድ አመራሮችና ሠራተኞች፣ እጅግ ባነሰ ደሞዝ ድርጅቱን ድርጅቴ ብለው 25 እና ከዚያ በላይ ላገለገሉ ሠራተኞች እንዲሁም በክብር በጡረታ ለተገለሉ ሠራተኞች ይህ የእውቅና መርሃግብር እንደተዘጋጀ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በአገራችን የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ያለባቸውን የግብዓት አቅርቦት ችግር ለመፍታት በዋናነት በኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት ስራ ላይ ተሰማራ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡