Job Vacancy - HR
Created 3/29/25
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት
ለውጭ አመልካቾች የወጣ ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም
ተ.ቁ. | የሥራ መደቡ መጠሪያ | ተፈላጊ ችሎታና አግባብነት ያለው የሥራ ልምድ | ብዛት | የሥራ ቦታ | ደመወዝ |
---|---|---|---|---|---|
1 | የሠራተኞች ሰርቪስ መኪና ሾፌር ደረጃ 8 | በአውቶ መካኒክ I ወይም 10ኛ ክፍል ያጠናቀቀ/ች እና 4ኛ ደረጃ መንጃ ፍቃድ/ ህዝብ ሁለት መንጃ ፍቃድ ያለው/ያላት እና 6/8 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ (ቱሉ ዲምቱ አካባቢ እና ጣፎ ሚሽን አካባቢ ላሉ ቅድሚያ ይሰጣል) | 2 | Head Office | 11808 |
ማሳሰቢያ፡-
. የሥራ መደቡ የቅጥር ሁኔታ በቋሚነት ነው፡፡
. የፈተና ጊዜና ቦታ በውስጥ ማስታወቂያ የሚለጠፍ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
. ሌቭል ለሚጠይቁ የሥራ መደብ COC ማቅረብ የግድ ነው፡፡
. ከዚህ በላይ በተጠየቀው መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 (ሰባት) ተከታታይ የሥራ
ቀናት የትምህርትና ሥራ ልምድ ማስረጃችሁን ዋናውን እንዲሁም የሕይወት ታሪክ መግለጫ ካሪኩለም ቪቴ (CV) በማያያዝ ዘወትር
በሥራ ሰዓት በግንባር በመቅረብ ወይም በድርጅቱ WWW.eiide.com.et ድረገጽ Tender-Job Vacancy በመላክ መመዝገብ የሚቻል
መሆኑን እንገልጻለን፡፡
አድራሻ፡- የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ) 1ኛ በር የሰው ኃብት አስተዳደር ቢሮ የቀድሞ ፒያሳ አትክልት ተራ
ከከሊፋ ህንጻ ትይዩ ባለው የባቡር መሻገሪያ ተሻግሮ ወደ ጣሊያን ሰፈር በሚወስደው መንገድ፤
ስልክ ቁጥር፡- 0113 69 22 13 ወይም 0113 69 26 10